top of page

ሐምሌ 17 2017 - በሴቶች ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ማህበራት ''ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግባቸው የለየናቸው ጉዳዮች ትኩረትም እንዲደረግባቸው'' ሲሉ ጠየቁ

  • sheger1021fm
  • Jul 24
  • 1 min read

በሴቶች ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ማህበራት ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግባቸው የለየናቸው ጉዳዮች እንዳይወጡ፣ ትኩረትም እንዲደረግባቸው ሲሉ ጠየቁ፡፡


የሀገራዊ ምክክሩ በበኩሉ የሴቶች ጉዳይ ትኩረት የማያገኝበት ምንም ምክንያት የለም ሲል አስረድቷል፡፡


የሴቶች ማህበራቱ ዋና ዋና እና አንገብጋቢ ናቸው ብለው ለኮሚሽኑ ካስገባቸው አጀንዳዎች መካከል የሰላምና የፖለቲካ አለመረጋጋት የሚሉት ይገኙበታል፡፡

ree

የሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የመሬት ባለቤትነት መብት ውስንነት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የኑሮ ውድነትና የስራ አጥነት ችግር በሴቶች ላይ የሚፈጥረው ጫና ከብዙ በጥቂቶቹ ናቸው፡፡


የገቡት አጀንዳዎች አጀንዳ ብቻ ሆነው እንዳይቀሩ የሁሉም አካላትን ድጋፍ የሚጠይቅ ነው ሲሉ የሴቶቹ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ አሚን መሃመድ ተናግረዋል፡፡


የሴቶችን አጀንዳ ከተለያዩ ክልሎች ማሰባሰቡ ጠቀሜታው የጎላ ቢሆንም ሴትን የተመለከቱ አጀንዳዎች ትኩረት ሲሰጣቸው አይታይም ያሉት ደግሞ የጥምረት ለሴቶች በሃገራዊ ምክክር መድረክ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሳባ ገ/መድህን ናቸው፡፡


የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በበኩሉ ኮሚሽኑ ትኩረት ያስፈልጋቸዋል ካላቸው መካከል ሴቶች፣ አካል፣ ጉዳተኞችና ወጣቶች መሆናቸውን ተናግሯል።


በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት የሴቶች አጀንዳ በአግባቡ እንዲካተት ሲሰራ የነበረው ኮሚሽኑ የአጀንዳ ቀረፃ ሲካሄድ ትኩረት እንዳያገኙ የሚያደርግበት ምክንያት የለውም ሲሉ ነገሩን የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጥበቡ ታደሰ ናቸው፡፡



ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page