ሐምሌ 17 2017 - በሴቶች ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ማህበራት ''ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግባቸው የለየናቸው ጉዳዮች ትኩረትም እንዲደረግባቸው'' ሲሉ ጠየቁ
- sheger1021fm
- Jul 24
- 1 min read
በሴቶች ላይ የሚሰሩ የተለያዩ ማህበራት ሀገራዊ ምክክር እንዲደረግባቸው የለየናቸው ጉዳዮች እንዳይወጡ፣ ትኩረትም እንዲደረግባቸው ሲሉ ጠየቁ፡፡
የሀገራዊ ምክክሩ በበኩሉ የሴቶች ጉዳይ ትኩረት የማያገኝበት ምንም ምክንያት የለም ሲል አስረድቷል፡፡
የሴቶች ማህበራቱ ዋና ዋና እና አንገብጋቢ ናቸው ብለው ለኮሚሽኑ ካስገባቸው አጀንዳዎች መካከል የሰላምና የፖለቲካ አለመረጋጋት የሚሉት ይገኙበታል፡፡

የሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትና የመሬት ባለቤትነት መብት ውስንነት፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የኑሮ ውድነትና የስራ አጥነት ችግር በሴቶች ላይ የሚፈጥረው ጫና ከብዙ በጥቂቶቹ ናቸው፡፡
የገቡት አጀንዳዎች አጀንዳ ብቻ ሆነው እንዳይቀሩ የሁሉም አካላትን ድጋፍ የሚጠይቅ ነው ሲሉ የሴቶቹ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ አሚን መሃመድ ተናግረዋል፡፡
የሴቶችን አጀንዳ ከተለያዩ ክልሎች ማሰባሰቡ ጠቀሜታው የጎላ ቢሆንም ሴትን የተመለከቱ አጀንዳዎች ትኩረት ሲሰጣቸው አይታይም ያሉት ደግሞ የጥምረት ለሴቶች በሃገራዊ ምክክር መድረክ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሳባ ገ/መድህን ናቸው፡፡
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በበኩሉ ኮሚሽኑ ትኩረት ያስፈልጋቸዋል ካላቸው መካከል ሴቶች፣ አካል፣ ጉዳተኞችና ወጣቶች መሆናቸውን ተናግሯል።
በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት የሴቶች አጀንዳ በአግባቡ እንዲካተት ሲሰራ የነበረው ኮሚሽኑ የአጀንዳ ቀረፃ ሲካሄድ ትኩረት እንዳያገኙ የሚያደርግበት ምክንያት የለውም ሲሉ ነገሩን የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ጥበቡ ታደሰ ናቸው፡፡
ማርታ በቀለ












Comments