ሐምሌ 11 2017 - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ከትግራይ ክልል ከተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ጋር በክልሉ ጉዳይ ዙሪያ መምከራቸው ተነገረ
- sheger1021fm
- Jul 18
- 1 min read



የክልሉ ሰላም፣የተፈናቃዮች ሁኔታ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ምክክር ከተደረገባቸው ውስጥ መሆናቸው ተወርቷል።
የፌዴራል መንግስት ችግሮችን በሽምግልና እና በምክክር ለመፍታት ቅድሚያ እንደሚሰጥ በተግባር አሳይተናል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክክሩን ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በትግርኛ ቋንቋ ባጋሩት ፅሁፍ።
በዚሁ ስብሰባ ላይ የፕሪቶሪያው ስምምነት አፈፃፀም ላይ አሉ የተባሉ ጉድለቶች እንዲታረሙም ተጠይቋል ተብሏል።
ከቃላት አጠቃቀም ጀምሮ የሚታዩ ችግሮች እንዲታረሙ የትግራይ ክልል እና ህዝብም ጦርነቱ ካስከተለበት ጉዳት አገግሞ ወደ መደበኛ ህይወቱ እንዲመለስ ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ዙሪያም መነጋገራቸውን አብራርተዋል።
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments