ሐምሌ 10 2017 - ምሁራን በጥናትና ምርምር ደረስንበት ብለው የሚያወጡት የጥናት ውጤት ምን ያህል የፖሊሲ ግብዓት ይሆናል?
- sheger1021fm
- Jul 17
- 1 min read
በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ በየጊዜው ምርምር የሚያደርገው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሲዬሽን በምርምር ስራዎቹ ዙሪያ የሚመክርበት 22ኛ ጉባኤውን ለማድረግ እየተሰናዳ ነው።
የኢትዮጵያ የኢኮኖሚክስ አሶሼሽን በዘንድሮው ዓለም አቀፍ ጉባኤው በዝቅተኛ የደመወዝ ወለል፣ በኢትዮጵያ የታክስ ሥርዓትና በሌሎች ከ10 በላይ የሚሆኑ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ ጥናትና ምርምር እንደሚያቀርብ ሰምተናል።
ጉምቱ የማክሮ ኢኮኖሚ ተመራማሪዎች የሚሰጡት የምርምር እና የጥናት ወረቀቶችን ፤ መንግስት ተቀብሎ ለፖሊሲ ግብአት ይጠቀምበታል ወይ ተብሎ ይጠየቃል።
ውሳኔ አሳላፊዎች ፖሊሲ ቀራጮች ከዚህ ቤት የወጣውን እና በብርቱ የተደከመበትን የምርምር ውጤት ቢጠቀሙት ይበጃል ተብሎም ሲመከር ይሰማል።
ለመሆኑ እስካሁን የተሰሩ ምርምሮችና ውጤቶቹ ምን ያህል የፖሊሲ ግብዓት ሆነዋል፤ የምታቀርቡት ምክረ ሀሳብስ ከሀሳብ አልፎ ተግባራዊ እየተደረገ ነው ወይ? ብለን ጠይቀናል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……..
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s








