top of page

ነሐሴ 8፣2016 - መንግስት ኢትዮጵያ ላይ አንባቢ ትውልድ እንዲጠፋ እያደረገ ነው ተባለ

  • sheger1021fm
  • Aug 14, 2024
  • 1 min read

መንግስት ኢትዮጵያ ላይ አንባቢ ትውልድ እንዲጠፋ እያደረገ ነው ተባለ።

 

ይህ የተባለው የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በመፅሐፍት ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ መጨመሩን ተከትሎ ባደረግው ውይይት ላይ ነው።

 

በወመዘክር መፃህፍት ቤት አንጋፋ ደራሲያን፣ አሳታሚዎች፣ የህግ ባለሙያዎች በተገኙበት በተደረገው ውይይት ከዚህ በፊት የነበሩ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች መፅሐፍት ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ እንዲሆን አድርገው እንደነበር ማህበሩ ጠቅሷል፡፡

 

አሁን ያለው መንግስት ግን በመፅሐፍት ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲጣል አድርጓል ብሏል።

 

በመንግስት አካባቢ በድርሰት የሚታወቁ ሰዎች ቢኖሩም ችግሩን እያወቁ ችላ ብለውታል ተብሏል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት መንግስት አብያተ መፅሐፍት እና ትምህርት ቤት እየገነባ ቢሆንም መፅሀፍት ግን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርብ እያደረገ አይደለም ይህም የሚቃረን ስራ ነው ተብሏል።

 

በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ደራሲያን እንዳሉት መፅሐፍት በመንግስት መደጎም እያለበት ጭራሽ እንዲጠፋ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

 

ከዚህ ባለፈም አንባቢ እንዲጠፋ መንግስት ይፈልጋልን? ብለው የሚጠይቁት የውይይቱ ተሳታፊዎች ይህንንም የሚያደርገው ጠያቂ ትውልድ ስለማይፈልግ ነው ሲሉ ግምታቸውን ሰምተዋል፡፡

 

የዲጂታል ቴክኖሎጂ አይቀሬ ከመሆኑም በላይ ለሀገር ጠቃሚ መሆኑ አይካድም፡፡

 

 ነገር ግን ትውልዱ መፅሐፍት ታትሞ እንዲያነብና እንዲመራመር ካልተደረገ እሮቦት የሆነ ትውልድ ለሀገር ከማፍራት አይተናነስም ሲሉ ደራሲያኑ አሳስበዋል።

አሁን ባለው የኑሮ ውድነት ምክንያትና የህትመት ዋጋ መናር ምክንያት ደራሲያን ከድርሰት ስራ ወጥተው በድለላ ስራ እየተሰማሩ መሆኑ በውይይቱ ተነስቷል።

 

መንግስት አንባቢ ትውልድ እንዲፈጠርና እውቀት እንደሀገር እንዲሰፋ ይህን የመፅሐፍት ተጨማሪ እሴት ታክስ ሊያነሳው ይገባል ሲል የደራሱያን ማህበሩ አሳስቧል።

 

በረከት አካሉ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page