top of page

ታህሳስ 7፣2017 - ሀብት ማስመዝገብን የመንግስት ተሿሚዎች ብቻ ሳይሆን የግል ተቋማት እና ሰዎችም ያስመዘግባሉ ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Dec 16, 2024
  • 1 min read

ሌብነትን ወይም ሙስናን ለማስቀረት በሚል የሀብት ማስመዝገብ ስራ ከ14 ዓመታት በፊት መጀመሩ ይታወሳል፡፡


የሀብት ምዝገባውም ከወረቀት አሰራር ወደ ኢንተርኔት መላ ተሸጋግሯል ተብሎም ነበር፡፡


በህንዳዊያን የተሰራ የኦንላይን #ሀብት_ማስመዝገብ መላ ግን ጥቂት ዓመታት ሰርቶ ተቋርጦ ቆይቷል፡፡


አሁን በስራ ላይ የዋለው መተግበሪያ በኢትዮጵያውያን የተሰራ ነው ተብሏል፡፡


ቴክኖሎጂው ሀብትን ከመዘገበ በኋላ ማረጋጋጫ ሰርተፍኬት እንደሚሰጥ ከፌዴራል #የፀረ_ሙስና ኮሚሽን ሰምተናል፡፡


ሀብት ማስመዝገብን የመንግስት ተሿሚዎች፣ ተመራጮች ብቻ ሳይሆን የግል ተቋማት እና ሰዎችም ያስመዘግባሉ ተብሏል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://t.ly/9uH-g


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page