top of page

ሐምሌ 28፣2015 - ምርቶቹን የሚጠቀሙ የሴቶች ቁጥር 25 በመቶ ብቻ መሆናቸው ጥናት አሳይቷል


በኢትዮጵያ የሴት ልጅ የተፈጥሮ ዑደት የሆነው የወር አበባ ከነውር መቆጠሩ አሁንም አልቀረም።


በተለይ ትምህርት ባልተስፋፋበት፣ ሴቶች ዕድሜያቸው ለአካለ መጠን ሳይደርሱ ለጋብቻ በሚታጩበት የገጠሩ ማኅበረሰብ ውስጥ የወር አበባ ጉዳይ ሸክሙ ይከብዳል።


ልጃገረዶች በትምህርት ቤት ሳሉ ድንገት የወር አበባቸው መጥቶ ደም ቢፈሳቸው፤ "አይዞሽ" ከመባል ይልቅ መሳቂያ፣ መሳለቂያና ጣት መጠቋቆሚያ ይሆናሉ።


ይህን በመፍራት ብዙ ልጃገረዶች ገና የወር አበባቸው መምጫ መቃረቡን ሲያስቡ ይሸበራሉ፣ ከትምህርት ቤትም ይቀራሉ፣ ትምህርታቸው ለብዙ ቀናት ይስተጓጎላል፤ በዚያው መጠን ከትምህርቱ ወደኋላ ይቀራሉ።


መንግሥትም ሞዴስ በሀገር ውስጥ የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ከውጭ ለሚያስገቡት ጥሬ እቃ ከታክስ ነፃ እንዲሆኑ ንፅህና መጠበቂያዎቹ ከውጭ ሲገቡ ደግሞ ታክሱ 10 ከመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል፡፡


ዋጋው በመወደዱ ምክንያት ምርቶቹን የሚጠቀሙ የሴቶች ቁጥር 25 በመቶ ብቻ መሆናቸው ጥናት አሳይቷል፡፡


በረከት አካሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2024 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page