top of page

ሐምሌ 28፣2015 - ምርቶቹን የሚጠቀሙ የሴቶች ቁጥር 25 በመቶ ብቻ መሆናቸው ጥናት አሳይቷል

  • Aug 4, 2023
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የሴት ልጅ የተፈጥሮ ዑደት የሆነው የወር አበባ ከነውር መቆጠሩ አሁንም አልቀረም።


በተለይ ትምህርት ባልተስፋፋበት፣ ሴቶች ዕድሜያቸው ለአካለ መጠን ሳይደርሱ ለጋብቻ በሚታጩበት የገጠሩ ማኅበረሰብ ውስጥ የወር አበባ ጉዳይ ሸክሙ ይከብዳል።


ልጃገረዶች በትምህርት ቤት ሳሉ ድንገት የወር አበባቸው መጥቶ ደም ቢፈሳቸው፤ "አይዞሽ" ከመባል ይልቅ መሳቂያ፣ መሳለቂያና ጣት መጠቋቆሚያ ይሆናሉ።


ይህን በመፍራት ብዙ ልጃገረዶች ገና የወር አበባቸው መምጫ መቃረቡን ሲያስቡ ይሸበራሉ፣ ከትምህርት ቤትም ይቀራሉ፣ ትምህርታቸው ለብዙ ቀናት ይስተጓጎላል፤ በዚያው መጠን ከትምህርቱ ወደኋላ ይቀራሉ።


መንግሥትም ሞዴስ በሀገር ውስጥ የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ከውጭ ለሚያስገቡት ጥሬ እቃ ከታክስ ነፃ እንዲሆኑ ንፅህና መጠበቂያዎቹ ከውጭ ሲገቡ ደግሞ ታክሱ 10 ከመቶ እንዲሆን መወሰኑ ይታወሳል፡፡


ዋጋው በመወደዱ ምክንያት ምርቶቹን የሚጠቀሙ የሴቶች ቁጥር 25 በመቶ ብቻ መሆናቸው ጥናት አሳይቷል፡፡


በረከት አካሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የሐምሌ 15 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሞሪታንያ በሞሪታንያ የባህር ዳርቻ አቅራቢያ በደረሰ የባህር አደጋ 144 ጥገኝነት ፈላጊዎቹ ሳይሞቱ አልቀረም ተባለ፡፡ የአደጋው ሟቾች መነሻዋን ከጋምቢያ በማድረግ ወደ ስፔን በማምራት ላይ በነበረች ጀልባ የተሳፈሩ ጥገኝነት ፈላጊዎች እንደሆኑ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በጀልባዋ ተሳፍረው የነበሩት በሙሉ ከተለያዩ የአፍ

 
 
 
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡

ሐምሌ 15 2018 በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት ወይም ማቆያዎች ላይ ለውጦች እየመጡ ነው ተባለ፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት የህፃናት ማቆያዎቹ ጥቂት ነበሩ ያለው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አሁን ላይ ከፍተኛ መሻሻሎች ታይተውበታል ብሏል፡፡ ጥናቱም በግል እና በመንግስት ማ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page