top of page

ሚያዝያ 21፣2016 - የ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ

  • sheger1021fm
  • Apr 29, 2024
  • 1 min read

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2016 የትምህርት ዘመን የ12ተኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀንን ይፋ አድርጓል፡፡


ፈተናው ለማህበራዊ ሳይንስ ከሐምሌ 3-5 እንዲሁም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ከሐምሌ 9-11 በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል ተብሏል።


በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30- ሐምሌ 01/2016 ድረስ እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት አለባቸው ሲል አሳስቧል።


ስለሆነም ተፈታኞች እና የሚመለከታቸው ሁሉ በወጣው ቀነገደብ መሰረት ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ እናሳስባለን ሲል አገልግሎቱ ባወጣው መረጃ ተናግሯል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Telegram: @ShegerFMRadio102_1




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page