top of page

መጋቢት 4 2017 - በሰሜን ወሎ ዞን የቡግና ወረዳ ነዋሪ የምግብ ድጋፍ ካገኙ ከሀያ ቀን በላይ ሆኗቸዋል ተባለ

Updated: 3 days ago

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የቡግና ወረዳ ነዋሪ የምግብ ድጋፍ ካገኙ ከሀያ ቀን በላይ ሆኗቸዋል ተባለ፡፡


ከወራት በፊት በዞኑ ረሀብ ጠንቶ መክረሙን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲነገር መቆየቱን ተከትሎ መንግስትም፣ ህዝቡም ሆነ ረጅ ድርጅቶች ድጋፍ ማድረግ እንደጀመሩ የሚዘነጋ አይደለም፡፡


ነገር ግን ከሀያ ቀናት በፊት በመንግስትም ሆነ በረጅ ድርጅቶች ይደረግ የነበረው ድጋፍ መቋረጡን የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ፅህፈት ቤት ነግሮናል፡፡


ባለፈው የክረምት ወቅት ባጋጠመ የዝናብ እጥረት የምርት አቅርቦት ችግር እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል በዚህም ደግሞ ነዋሪው ለምግብ እጥረት ተጋልጧል፡፡


አጠቃላይ አመርታለሁ ብሎ ካቀደው 294 ሺህ ኩንታል፤ 91 ሺህ ኩንታል ብቻ መመረቱ የተነገረ ሲሆን ይመረታል ተብሎ በእቅድ ከተያዘው 30 በመቶ ገደማው ብቻ እንደተገኘ የወረዳው የግብርና ፅህፈት ቤት መናገሩ የሚታወስ ነው፡፡


በዞኑ የተፈጠረውን የምግብ እጥረትም ለአለም ህዝብ እንዲደርስ በማድረግ እርዳታዎች ማግኘት ጀምረን ነበር የሚሉት የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ አለሙ ይመር ድጋፉ ከተቋረጠም 20 ቀን አልፏል ይላሉ፡፡


ለዚህም አንደኛው ምክንያት የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID) ስራ ማቆሙ ነው ብለዋል፡፡


በሌላ በኩል ክልሎች ራሳቸውን ችለው ችግር ያለባቸውን ነዋሪዎች ያግዙ በመባሉ ነው ተብሏል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ…







ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page