top of page

መስከረም - 13፣2017 - በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ያሉበት የዲፕሎማቲክ አጀባ(ኮንቮይ) ላይ የሽብር ጥቃት ተፈፀመ

በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ያሉበት የዲፕሎማቲክ አጀባ(ኮንቮይ) ላይ የሽብር ጥቃት ተፈፀመ፡፡


አምባሳደር ጀማል በኸር ያሉበት የዲፕሎማቲክ ኮንቮይ ላይ ጥቃት የደረሰው በፓኪስታን ፓክቱንክዋ ክልል መሆኑንን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡


የዲፕሎማቲክ አጀቡ የሌሎች ሀገሮች ዲፕሎማቶች ያሉበት እንደነበርም ተጠቅሷል፡፡


የሽብር ጥቃቱን ያወገዘው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በጥቃቱም የኢትዮጵያ ዲፕሎማት ከሚያጅቡት ውስጥ አንደኛው ህይወቱ ማለፉን አስረድቷል፡፡


ጥቃቱን ያወገዘው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለፓኪስታን ህዝብ እና መንግስትም መፅናናትን እመኛለሁ ብሏል፡፡


በዲፕልማቶቹ ላይ የሽብር ጥቃት የተፈፀመባቸው ትናንት እሁድ በአካባቢው ያለን የቱሪስት ቦታ ለመጎብኘት ጉዞ ላይ በነበሩበት ወቅት መሆኑ ተሰምቷል፡፡


በቦምብ በተፈፀመው ጥቃት በዲፕሎማቶቹ ላይ ምንም ጉዳይ አልደረሰም ሲል ሮይተርስ የሀገሪቱን ባለስልጣናት ተጠቅሶ ዘግቧል፡፡


በመንገድ ላይ በተቀበረው ቦምብ ለተፈፀመው የሽብር ጥቃት ሀላፊነቱን የወሰደ ወገን የለም፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page