top of page

ጥር 6፣2017 - ''ድህነትን የሚያባብስና ዜጎችን ለተደራራቢ የወጪ ጫና የሚዳርግ ነው'' በሚል ሲያከራክር የነበረው የንብረት ታክስ አዋጅ ፀደቀ

  • sheger1021fm
  • Jan 14
  • 1 min read

ድህነትን የሚያባብስና ዜጎችን ለተደራራቢ የወጪ ጫና የሚዳርግ ነው በሚል ሲያከራክር የነበረው የንብረት ታክስ አዋጅ ፀደቀ፡፡


የህንፃዎች የገበያ ዋጋ ተገምቶ የዋጋው 25 በመቶውን መነሻ በማድረግ ታክስ እንዲከፈልበት የሚያስገድደው የንብረት ታክስ አዋጅ የመንግስት ተቋማትን እና በጎ አድራጊ ድርጅቶችን ከታክስ ነፃ አድርጓል፡፡


የሃይማኖት ተቋማትም ለአምልኮ እና ለቀብር አገልግሎት የሚጠቀሙባቸው ህንፃዎች ብቻ #የንብረት _ክስ እንደማይከፈልባቸው ተነግሯል፡፡

ree

በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ዛሬ አዋጁ ሲፀድቅ እንደሰማነው የዝቅተኛ ገቢ ባለቤት የሆነ የአንድ ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ያለው ታክስ አይከፍልም ይላል አዋጁ፡፡


ይሁንና ዝቅተኛ ገቢ ያለው ማን ነው? የሚለው አለመወሰኑ አሻሚ ያደርገዋል ሲሉ የፓርላማ አባላት አንስተዋል፡፡


ከባንክ ብድር ወስዶ መኖሪያ የገነባ #የመንግስት_ሰራተኛ ከደመወዙ 35 በመቶ የገቢ ግብር ተቆርጦበት የሊዝ የጣሪያና የግድግዳ ግብር ከፍሎ፣ የአከራይ ተከራይ ተቆርጦበት፣ በዚያ ላይ የባንክ ወለድና ብድር እየከፈለ የንብረት ታክስ ቢጣልበት መክፈል ይችላል ወይ? ሲሉ እንደራሴዎች ጠይቀዋል፡፡


ብዙ ያከራከረው ይኸው አዋጅ በ4 ተቃውሞ፣ በ10 ድምፀ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ… https://tinyurl.com/yc4eb9hz


ትዕግስት ዘሪሁን

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page