ጥር 21 2017 - የአለም ሎሬት ሜተር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ እና ስቲዲዮ የነበረው ቪላ አልፋ ከአራት ወራት ብኋላ ለህዝብ ክፍት ሊደረግ ነው
- sheger1021fm
- Jan 29
- 1 min read
የአለም ሎሬት ሜተር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መኖሪያ እና ስቲዲዮ የነበረው ቪላ አልፋ ከአራት ወራት ብኋላ ለህዝብ ክፍት ሊደረግ ነው።
በአዲስ አበባ ጦር ሀይሎች አካባቢ የሚገኘው ቪላ አልፋ ከጣሪያው ጀምሮ ወደ ምድር የሚዘልቀው ፍሳሽ የእድሳት ጉዞውን ረጅም እና እድካሚ እንዳደረገው ታውቋል።
ነገር ግን በሁለት ወር ውስጥ ቀሪው ስራ እና የሙዚየም ስራው ተጠናቆ በአራት ወር ውስጥ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን የቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባ አያሌው ነግረውናል።

ህዝብ በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የአርቲስቱ መኖሪያ ቪላ አልፋ ከዛሬ ነገ በቅርቡ ክፍት ይሆናል ሲባል ቆይቷል።
ለመሆኑ ከወሰን ማካለል እና አካባቢው መኖሪያ መሃል እንደመሆኑ መጠን በዚህ ሐሳብ መንገድ ምን ተሰራ ብለን የጠየቅናቸው ኃላፊው የሙዚየሙ አጎራባች እንደተለየና ለጉብኝት አመቺ ተደርጎ እንደታደሰ ነግረውናል።
የአለም ሊቀ ሊቃውንት የኪነ ጥበብ ባለሙያው ሰአሊ አፈወርቅ ተክሌ የእጅ ስራዎች መካከል መናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የግድግዳና ጣሪያ ስዕሎች፣ የሞዛይክ ስራዎች፣ የመስኮትና መስታወት ስዕሎች፣ የዳግማዊ የምፅአት ፍርድ፣ የደመራ ስእል፣ የራስ መኮንን ሀውልት፣ የአፍሪካ ድል አፍሪካ አጠቃላይ ነጻነት፣ የመስቀል አበባ እንዲሁም እናት ኢትዮጵያ ይገኙበታል።
ተህቦ ንጉሴ











Comments