top of page

ጥር 19፣2017 - የሴቶች ጥቃት ተደጋግሞ በመሰማቱም የየዕለት ተግባር የሆነ ይመስላል ምን ይሻላል?

  • sheger1021fm
  • Jan 27
  • 1 min read

በቤተሰብ አባል፣ በአባት፣ በወንድም የአስገድዶ መደፈር ወንጀል የሚፈጸምባቸው በወንድ ጓደኞቻቸው እና የትዳር አጋር ከባድ የአካል ጉዳትና እስከሞት የደረሰ ጉዳት የሚደርስባቸው ሴቶች ቁጥር በርክቷል፡፡


ወንጀሉ ተደጋግሞ በመሰማቱም የየዕለት ተግባር የሆነ ይመስላል፡፡


ይህ በሴቶች ላይ የሚፈጸመው የ #ጾታዊ_ጥቃት ወንጀል እንዲህ ተደጋግሞ ቢሰማም በአግባቡ በህግ ፊት ተጠያቂ የሚሆኑት ወንጀለኞች ግን ተገቢውን ቅጣት ሲያገኙ አይታይም፡፡


ይህም ወንጀሉ የተለመደ ይመስል እንዲደጋገም እያደረገ ነው ለዚህም የሀገሪቱ የወንጀል ህግ በአጥፊዎች ላይ የሚጥለው ቅጣት በቂ ባለመሆኑ ነው ሲሉ የስርዓተ ጾታ መብት ተሟጋቾች እና የህግ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡


ከሀና ላላንጎ እስከ ህፃን ሄቨን በሴቶች በህፃናት ላይ የተፈፀሙ፣ ለጆሮ የሚከብዱ ጥቃቶች በተደጋጋሚ እያጋጠመ ነው፡፡


ለጥቃቱ መጨመር በአጥፊዎቹ ላይ የሚጣለው ቅጣት አነስተኛ መሆኑ ነው በሚል ይነሳል፡፡


ታድያ ምን ይሻላል?



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page