top of page

ጥር 17 2017 - የኢትዮጵያ ከሶስት ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጥ ልትጀምር ነው

  • sheger1021fm
  • Jan 25
  • 1 min read

የኢትዮጵያ ከሶስት ወር በኋላ ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጥ ልትጀምር ነው፡፡


በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ ከሚያዚያ ወር ጀምሮ ለታንዛኒያ 100 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጥ ትጀምራለች ተብሏል፡፡


ይህን የሚያስችለወን ስምምነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የታንዛኒያ የኤሌክትሪክ አቅራቢ ኩባንያ እና የኬንያ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ የሦስትዮሽ የኃይል ሽያጭ ድርድር ስምምነት ማድረጋቸው ተሰምቷል።


ስምምነቱ በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ላይ ያተኮሩ የህግ፣ የኮሜርሻል እና የቴክኒክ ጉዳዮች ላይ መሠረት ያደረገ እንደሆነ ተነግሯል፡፡


ስመነቱም ከታንዛኒያ ጋር የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ኬንያ ከታንዛንያ ጋር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የኪራይ ውል ሥምምነት መሆኑንን የኢትዮጵያ ኤልክትሪክ ሃይል ተናግሯል።


የሦስትዮሽ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ለታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ለማከናወን የሚያስችላትን መብት የሚሰጣት መሆኑንም ተጠቅሷል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page