top of page

ጥር  12፣ 2017 - የአዕምሮ እድገት ውስንነት እና የአካል ጉዳት ያለባቸው ህፃናት የት ይማሩ?

  • sheger1021fm
  • Jan 20
  • 2 min read

የአዕምሮ እድገት ውስንነት እና የአካል ጉዳት ያለባቸው ልጆቻችንን ይዘን ወደ መንግስትም ሆነ የግል ትምህርት ቤቶች ስንሄድ፤ ትምህርት ቤቶቹ እንቀበልም ይሉናል በማለት ወላጆች በተደጋጋሚ ሲናገሩ ይሰማሉ፡፡

 

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በበኩሉ፤ በኢትዮጵያ ካሉ አካል ጉዳተኛ ህፃናት ከ85 እስከ 90 በመቶዎቹ የትምህርት እድል አያገኙም ሲል ባሳለፍነው ታህሳስ ወር ላይ ተናግሮ ነበር፡፡

 

የአዲስ አባባ አካል ጉዳተኞች ማህበርም ት/ት ቤቶች ልጆቹን አንቀበልም በማለታቸው ወላጆች እየተማረሩ ናቸው ብሎናል፡፡ የማህበሩ ፕሬዚደንት ወይንሸት ግርማ (ዶ/ር) እነዚህ ወላጆች ተሰብስበው ክስ ቢመሰርቱ ተቀባይነት አላቸው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ree

ታዳጊ ሀያት ከድር፤ ‘’አንድንት የአዲስ አባባ አካል ጉዳተኛ ህጻናት ማህበር’’ ሰብሳቢ ናት፡፡ አካ ጉዳተኛ ህጻናትና ታዳጊዎች የበዙ ችግሮች እንደሚገጥሟቸው ታነሳለች፡፡ ትምህርት ቤት የገቡትም ቢሆን የመማሪያ ቁሳቁሶች ስለማይሟሉላቸው በተገቢው ትምህርቱን ይማራሉ ማለት እንደማይቻልም ትናገራለች፡፡

 

በተጨማሪም በርካታ ወላጆች የአካል ጉዳት እና የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ልጆቻቸውን በግንዛቤ ችግር የተነሳ እንኳንስ ትምህርት ቤት ሊወስዷቸው ይቅርና ከቤት አያስወጧቸውም ብላናልች፡፡

 

በአካል ጉዳተኛ ህፃናት እና ሴቶች ዙሪያ የሚሰራው ‘’የራስ አገዝ ቡድን አሠራር፣ ድርጅቶች ኅብረት (ኮሳፕ)’’ ድርጅት ስራ አስኪያጅ፤ ዮሴፍ አካሉ አሁን በረቂቅ ደረጃ ያለውና አካል ጉዳተኞችን የተመለከተው አዋጅ የአካል ጉዳተኞችን መብት የሚጥሱትን ተጠያቂ የሚያደርግ መሆን አለበት ብለውናል፡፡

ree

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ፤ ጉዳዩ ከሚመመለከታቸው ተቋማት መካካል አንዱ የሆነው የአዲስ አበባ ሴቶች፣ ህጻናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮን በጠይቀናል፡፡ በቢሮው የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋዊያን ግንዛቤ ስርጸት እና ንቅናቄ ብድን መሪ አየሁ ደመቀ፤ ትምህርት ቤቶች እነዚህን ልጆች እንቀበልም እንደሚሉ መረጃዎች ይደርሱናል እኛም እናውቃለን ብለውናል፡፡

 

ይህ የሆነውም ተጠያቂነት ስላለሰፈነ እንደሆንም ጠቅሰዋል፡፡ ችግሩ ለአንድ አካል የሚተው ጉዳይ ሳይሆን ሁሉም በያገባኛል ሊሰራበት የሚገባ ነውም ይላሉ ሀላፊዋ፡፡ አሁን እነዚህን ልጆች አንቀበልም የሚሉ አካላት ነገ ከነገ ወዲያ የእነሱ ልጆች መሰል ችግር እንደማያጋጥማቸው ምን ዋስትና አላቸው ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡

ree

ከላይ ለተነሳው ችግር በመንግስት እንደ መፍትሄ እየተሰራበት ያለው የአካቶ ትምህርትን ነው፡፡ ይህ የአካቶ ትምህርት ተግባራዊነቱ ምን ያህል ነው ያልናቸው ወ/ሮ አየሁ ለውጦች አሉ ግን በሚፈለገው ደረጃ ግን አይደለም ሲሉም መልሰዋል፡፡

 

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ ህጻናቱን ለምድነው እንቀበልም የምትሉት ብዬ ትህርት ቤቶቹን ስጠይቃቸው፤ የመማሪያ ቦታ፣ የመምህር ባጠቃላይ የአቅም ችግር ስላለብን ነው ብለውኛል ማለቱም የታወሳል፡፡

 

ነገር ግን ትምህርት ቤቶቹ የያቀረቡልኝ ምክንያት አላሳመነኝም፤ ብሎ ነበር በወቅቱ ኢሰመኮ፡፡

 

ማንያዘዋል ጌታሁን

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page