top of page

ጥር 1፣2017 - አዋጁ በነዳጅ ግብይት ላይ የሚታየውን ‘’መሰረታዊ ችግር ከመፍታት ይልቅ ቅጣት ላይ ያተኮረ ነው’’ የሚል ትችት ቀርቦበታል

  • sheger1021fm
  • Jan 9
  • 1 min read

ዛሬም ድረስ በኢትዮጵያ ወደ 500 ወረዳዎች የነዳጅ ማደያ የላቸውም ተባለ፡፡


ይህን ያለው የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ነው፡፡


የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የነዳጅ ውጤቶች ግብይትን ሥርዓት ለመደንገግ የተዘጋጀው #አዋጅ ላይ ለማፅደቅ በጠራው መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው ይህን የተናገሩት፡፡


ዳይሬክተሯ ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት እና እኛ ካለን የህዝብ ብዛት መጠን ያለን የነዳጅ ማደያ ዝቅተኛ ነው ብለዋል፡፡


#የነዳጅ_ማደያ ግንባታ እየተካሄደ ያለው ጠረፍና ምንም የኢኮኖሚ ፋይዳ በሌለባቸው አካባቢዎች መሆኑ ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡

ree

የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በዛሬው እለት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት ለመደንገግ የተዘጋጀውን አዋጅ የሰላ ትችት ቢቀርብበትም በአበላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡


አዋጁ በነዳጅ ግብይት ላይ የሚታየውን ‘’መሰረታዊ ችግር ከመፍታት ይልቅ ቅጣት ላይ ያተኮረ ነው’’ የሚል ትችት ቀርቦበታል፡፡


አዋጁ የተጋነነ ቅጣት በውስጡ የደነገገ መሆኑን የተናገሩት የምክር ቤት አባል ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ‘’ይህም በለሀብቱን እዳያሸማቅቅ ስጋት አለኝ ለምን አዋጁ ቅጣት ላይ ከማተኮር መሰረታዊ ችግሩን መፋታት ላይ አለተኮረም?’’ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡


ከሀገሪቱ ወንጀል ህጎች ጋር እንዳይጣረስ አዋጁ ታይቷል ወይ የሚልም ጥያቄም ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) አክለዋል፡፡

የባለስልጣኑ ዳይሬክተር ሳሃረላ አበዱላሂ በሰጡት ምላሽ ቅጣቱ የተጋነነ አንዳልሆነ ተናግረው በረቂቁ ላይ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካት ጋርም ተነጋግረናል ብለዋል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድመጡ…


ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
ታህሳስ 3/2018 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል። በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል። በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page