top of page

የካቲት 17 2017 - በአዲስ አበባ ከተማ በሸቀጦች ላይ የዋጋ መናር በተዳዳሚ ይስተዋላል

  • Feb 25, 2025
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ በሸቀጦች ላይ የዋጋ መናር በተዳዳሚ ይስተዋላል፡፡


ሸገር ራዲዮ በተለይ ስለ ዘይት ዋጋ ማሻቀብ እና በአንዳንድ ቦታዎች ምርቱ ከገበያ የመጥፋቱ ምክንያት ምንድነው ሲል የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮን ጠይቋል።


እንደማሳያም 5 ሊትር #ዘይት ከሁለት ሳምንታት በፊት ሲሸጥ ከነበረው ከ1100 እስከ 1200 በአንዴ ከ1480 እስከ 1700 ሲሸጥ ተመልክተናል፡፡


በአንዳንድ ሱቆች ደግሞ ምርቱ ስለተወደደ ከናካቴው መያዝ መተዋቸውን ነግረውናል፡፡


በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች አምስት ሊትር ዘይት ከ1480 እስከ 1700 ብር፣ ሶስት ሊትር ከ850 እስከ 900 ብር፣ አንድ ሊትር ደግሞ ከ300 እስከ 350 እተሸጠ እንዳለ ነጋዴዎቹ ነግረውናል፡፡


በሁለት ሳምንት ልዩነት በምግብ ዘይት ምርት ላይ እንዲህ ያለ የዋጋ ጭማሬ ማሳየቱ ለምን ይሆን፡፡


መፍትሄውስ ምንድነው ያልነው የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የዋጋ ጭማሪው በምን ምክንያት እንደተፈጠረ ለማወቅ ጥናት እያደረኩ ነው ብሏል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….




ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ።

መጋቢት 3/2018 በኢትዮጵያ የንግዱን ማህበረሰብ እየገጠሙ ካሉ ችግሮች 40 በመቶ ያህሉ ከገንዘብ አቅርቦት ጋር የተገናኙ ናቸው ተባለ ። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ 2 ሚሊየን የሚጠጉ ጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ኢንዱስትሪ ተቋማት እንዳሉ ተነግሯል። የእነዚህ ኢንዱስትሪ ባለቤቶችና ኢ-መደበኛ በሆኑ ሌሎች ንግ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page