top of page

የካቲት 14፣2016 - የገበያ ቅኝት - በሀገር ቤት ተመርቶ የሚቀርበው ጤፍ ለምን በዚህ ልክ ተወደደ?

  • sheger1021fm
  • Feb 22, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ከተማ የሸቀጦች ዋጋ መናር የነዋሪውን ህይወት እንደፈተነው ተደጋግሞ ይነገራል።


ከቅርብ ጊዝ ወዲህ ጤፍን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች በአንድ ጀንበር ዋጋቸው ከፍ ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡


ነገር ግን ከሰሞኑ የሽንኩርት እና የቲማቲም ዋጋ እቀነሰ ቢሆንም የጤፍ ዋጋ ጨምሯል፡፡


ጤፍ ከወራት በፊትም ከስድስት ሺህ ብር ወደ አስራ ሁለት ሺህ፣ አስራ ሶስት ሺህ እና አስራ አራት ሺህ ብር በአንድ ጊዜ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።


ሸገር በአንዳንድ ወፍጮ ቤቶች ተዘዋውሮ ጤፍ ሲገበያይ የሰነበተበትን ዋጋ ተመልክቷል፡፡


በዚህም በየደረጃው ከ135 ብር እስከ 145 ብር በኪሎ እየተሸጠ መሆኑን አይቷል፡፡


እዚሁ በሀገር ቤት ተመርቶ የሚቀርበው ጤፍ ለምን በዚህ ልክ ተወደደ?


ለምንስ የአቅርቦት እና የፍላጎት አለመጣጣም ሊያጋጥም ቻለ?


ሸገር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮን ጠይቋል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ።

በኦሮሚያ ክልል በሥራቅ አርሲ ዞን ባለንበት በጥቅምት ወር ብቻ 25 ሰዎች መገደላቸውን፣ ይህንንም የተመለከተው በከባድና ጥልቅ የኃዘን ስሜት መሆኑን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ተናገረ። ቋሚ ሲኖዶስ በኦሮሚያ  ክልል በምሥራቅ አርሲ ዞን አስተዳደር በጉና፣ በመርቲ፤ በሸርካ እና በሆሎንቆ ዋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page