top of page

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከሚያስተዳድራቸው ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የ22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት አሳየ፡፡

  • 4 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 11/2018


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከሚያስተዳድራቸው ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የ22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት አሳየ፡፡


በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የኤርፖርት መሰረተ ልማት ስራዎች እና ኤሮኖቲካል ያልሆኑ ገቢዎች አፈጻጸም ውጤታማነትን በተመለከተ በተሰራ ኦዲት 22 ኤርፖርቶች መሪ እቅድ ወይንም (Master Plan) እንደሌላቸው የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት ጠቅሷል፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የሚያስተዳድራቸው ኤርፖርቶች መሪ ዕቅድ (Master Plan)፣የመሬት አጠቃቀም ካርታ እና የይዞታ ካርታ ሊኖራቸው ይገባ ነበር ያለው ሪፖርቱ ነገር ግን ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በቀር የተቀሩት 22 ኤርፖርቶች የሌላቸውም ሲል አስረድቷል፡፡


ከተጠቀሱት ስምንት ኤርፖርቶች የመሬት አጠቃቀም ካርታ (Land Use Plan) የተዘጋጀላቸው ሲሆን፤ የተቀሩት 15 ኤርፖርቶች የመሬት አጠቃቀም ካርታ አልተዘጋጀላቸውም ብሏል መስሪያቤቱ ፡፡


ይይዞታ ካርታ የሌላቸው ሶስት አየር ማረፊያዎች እንዳሉ እና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታቸው ትክክለኛ ቦታውን አወሳኝ በሚያሳይ መልኩ ያልተሰራላቸው አራት የአየር ማረፊያዎች አሉ ተብሏል፡፡


በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት፣ በድሬደዋ እና በአሶሳ በኤርፖርቶቹ ዙሪያ የሚገኝ እስከ 13 ኪ.ሜ ስፋትያለው የመሬት አጠቃቀም ለአዕዋፋት መስህብ የተጋለጠ መሆኑን እና ይህም ለበረራ ስጋት የሚፈጥር እንደሆነ ዛሬ ለፓርላማ የቀረበው ባለ 65 ገጽ የኦዲተር መስሪያቤት ሪፖርት ጠቅሷል፡፡


የአሶሳ ኤርፖርት ግንባታ ቀድሞ የአዋጭነት ጥናት ባለመሰራቱ ኤርፖርቱ ከዋናው መንገድ አጠገብ በመሆኑ ተንቀሳቃሽ ነገሮች ለበረራ ስጋት መፍጠራቸውም በግኝት ተረጋግጧል፡፡


በተመሳሳይ የጎንደር አፄ ቴዎድሮስ ኤርፖርት የአየር መንግዱ ክልል አጥር ባለመታጠሩ እና ክፍት በመሆኑ እንስሳት እና ያልተፈቀደላቸው ሰዎች በቅጥር ግቢው እንደሚገቡ ተጠቅሷል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
አሐዱ ባንክ “አሐዱ ለኩሉ'' እና ''ማኅደር" የተባሉ ሁለት መተግበሪያዎችን በይፋ ስራ ማስጀመሩን ተናገረ።

ሰኔ 11/2018 አሐዱ ባንክ “አሐዱ ለኩሉ'' እና ''ማኅደር" የተባሉ ሁለት መተግበሪያዎችን በይፋ ስራ ማስጀመሩን ተናገረ። ሁለቱ የሞባይል መተግበሪያዎች የባንኩን የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎት ጉዞን ይበልጥ እንደያጠናክሩለት እንደሆኑ ተነግሯል። "አሐዱ ለከሉ "የተባለው የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ደንበኞች ሞባ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page