የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።
- sheger1021fm
- Jan 13
- 1 min read
ጥር 5/2018
የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በመንግስት አካላት እና በፖሊሲ አውጪዎች ላይ ጫና በማሳደር ስለ ትንባሆ አሳሳች መልክቶችን በማሰራጨት ንግዳቸውን ለማስፋፋት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።
ኢንዱስትሪዎቹ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ነን በሚል፣ የበጎ አድራጎት ስራን በማስታከክ እና በሌሎች ዘዴዎች የትምባሆ ስርጭትን ለማስፋፋት እየሰሩ ነው ተብሏል።
ከዚህ በተጨማሪም በዣንጥላዎች፣ በቲሸርቶች እና በመሰል ምርቶች ላይ ማስታወቂያዎችን እየሰሩ መሆኑም ተጠቅሷል።

የእነዚህን የኢንዱስትሪዎች ጫናን በመቋቋሙና ዘርፋን በመቆጣጠሩ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የተሻለ ስራ ሰርቻለሁ ብሏል።
በዓለም ዓቀፍ ደረጃ 100 ሀገራት በተካተቱበት ጥናት፤ ኢትዮጵያ የትምባሆ ምርቶችን በመቆጣጠሩ የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግባለች ተብሏል።
በዚህ ጥናት ኢትዮጵያ የትምባሆ ምርቶችን በመቆጣጠር ከአፍሪካ 2 ከዓለም ደግሞ 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች ሲል ተናግሯል።
ለዚህም ከአለም ጤና ድርጅት እውቅና ማግኘቱንም የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ዛሬ በሰጠው ማብራሪያ ተናግሯል።
ማንያዘዋል ጌታሁን












Comments