top of page

አማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ80000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ከ14000 በላይ የቁም እንስሳት መሞታቸውን የወረዳው ግብርና ቢሮ ተናገረ፡፡

  • 2 hours ago
  • 1 min read

ነሐሴ 5 2018


አማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ80000 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ከ14000 በላይ የቁም እንስሳት መሞታቸውን የወረዳው ግብርና ቢሮ ተናገረ፡፡




ከሚያዝያ አጋማሽ ጀምሮ ምንም ዓይነት ዝናብ ባለመጣሉ በወረዳው የሚገኙ 10 ቀበሌዎች ለከፍተኛ ድርቅ መጋለጣቸውና በዚህም ምክንያት ከ14000 በላይ የቁም እንስሳት መሞቻቸውን ሰምተናል፡፡


ከ80000 በላይ የሚሆኑ የማህበረሰብ ክፍል ጉዳት እንደደረሰባቸው በዚህም ድጋፍ እንደሚሹ የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ገዛአብ እያሱ ነግረውናል፡፡


ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ የጤና ችግሮች በቀበሌዎቹ እየታዩ እንደሆነም ሃላፊው ያስረዳሉ፡፡


ከጤናው ጋር ተያይዞ የሚታዩ ችግሮች በመኖራቸው የተከሰተው በሽታ ምን ይሆን? የሚለውን ለመለየት ይህንን የሚከታተል ግብረ ሀይል መቋቋሙንና አዲስ ጥናት እየተደረገ እንደሆነም አቶ ገዛአብ ነግረውናል፡፡


በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ9000 በላይ ሄክታር መሬት ላይ የተዘራ ሰብል መብቀል እንዳልቻለም ከሃላፊው ሰምተናል፡፡


አስቸኳይ የምግብ እና የውሃ እንዲሁም ለእንስሳት መኖ ለማቅረብ ያለው ሁኔታው ከወረዳው አቅም በላይ በመሆኑ የሌሎችም ድጋፍ እንሻለን፡፡


በዚህም መንግስታዊም ይሁን መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲያግዙት ወረዳው ጥሪውን አቅርቧል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ....




ማርታ በቀለ

Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ የባህል፣ የኪነ - ጥበብ እና የስፖርት ዘርፍ የአስተዳደር መዋቅር ወጥነት አለመኖር ፣ የመረጃ አያያዝ ችግር እና የሃብት ብክነት ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደጎዳው ጥናት አሳየ።

ነሐሴ 5 2018 በኢትዮጵያ የባህል፣ የኪነ - ጥበብ እና የስፖርት ዘርፍ የአስተዳደር መዋቅር ወጥነት አለመኖር ፣ የመረጃ አያያዝ ችግር እና የሃብት ብክነት ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንደጎዳው ጥናት አሳየ። ባህል እና ስፖርት በፌዴራል እና በክልል ደረጃ እንኳን ወጥ የሆነ አስተዳደራዊ መዋቅር እንደሌለው

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page