top of page

ታህሳስ 30፣2016 - ፈተና ከተቀመጡት አስተዳደር ሰራተኞች ግማሾቹ ወደቁ

  • Jan 9, 2024
  • 1 min read

ፈተና ከተቀመጡት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ግማሾቹ ወደቁ።


ፈተናውን የተፈተኑት 10,257 ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ 5,095 ዎቹ የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል፣ ቀሪዎቹ 50 በመቶ ደግሞ የተቀመጠውን የማለፊያ ነጥብ ማስመዝገብ አለመቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጣሰው ገብሬ ተናግረዋል።


ታህሳስ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ለከተማ አስተዳደሩ አመራር፣ ባለሞያዎች እና ሰራተኞች የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና መውሰዳቸው ይታወሳል።


መመዘኛ ፈተናውን የወሰዱ ዳይሬክተር እና ቡድን መሪዎች ቁጥር 4,213 ሲሆን የፈተናውን ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡት 34 በመቶ ወይም 1,422 የሚሆኑት ናቸው ተብሏል።


ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ቁጥር 681 የሚሆነው በተለያየ የስነ ምግባር ጥሰት ከፈተና ውጪ መሆናቸውን እና 441 የሚሆኑት ደግሞ በፈተና ስፍራ አልተገኙም መባሉን ሰምተናል።


በተጨማሪም በፈተናው ውጤት ላስመዘገቡ የክዋኔ ክህሎት ስልጠና ላላለፉት ደግሞ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደሚሰጥ እቅድ መያዙን ሀላፊው አስረድተዋል።




የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Recent Posts

See All
የሐምሌ 18 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ስፔን በስፔኗ ርዕሰ ከተማ ማድሪድ አቅረቢያ ነዋሪዎች በመዛመት ላይ በሚገኘው ከባድ የሰደድ እሳት ምክንያት ለቅቀው እንደወጡ ታዘዙ፡፡ የማድሪድ ምዕራባዊ ክፍል አቅራቢያ የሰደድ እሳቱ በጣሙን ያየለበት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ እስከ ትናንት ምሽትም ከ19 ሺህ በላይ ሰዎች ለቀው መውጣታቸው ተጠቅሷል፡፡ በስፔን ወቅታ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page