top of page

ታህሳስ 25፣2017 - የአዲስ አበበ ቄራዎች ድርጅት ለገና በዓል ከ4,000 በላይ የእንሰሳት እርድ ለመከወን ተዘጋጅቻለሁ አለ

  • sheger1021fm
  • Jan 3
  • 1 min read

የአዲስ አበበ ቄራዎች ድርጅት ለገና በዓል ከ4,000 በላይ የእንሰሳት እርድ ለመከወን ተዘጋጅቻለሁ አለ።


የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል ቅድመ ዝግጅታቸውን አስመልክቶ ዛሬ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች መግለጫ ሰጥተዋል።


በዚህም ወቀት ለበዓሉ ከ4,000 በላይ የቁም እንሰሳት ለማረድ ተዘጋጅተናል፤የሚያሳርዱት በአብዛኛው በከተማዋ ያሉ ልኳንዳ ቤቶች ናቸው ብለዋል።


ይሁንና ማንኛውም ግለሰብ ለበዓሉ የገዛቸውን የቁም እንሰሳት ወደ ቄራዎች ድርጅት ይዞ ቢመጣ የእንሰሳቱን ጤንነት በህክምና ባለመያዎች አረጋግጠን በተ ጣጣኝ ዋጋ የእርድ አገልግሎት እንሰጣለንም ብለዋል።


በዚህም መሰረት አንድ በሬ በ1470 ብር፣ በግና ፍየል ደግሞ በ165 እንደሚያርዱ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ አንስተዋል።

ree

በተጨማሪም ስጋን በኪሎ መግዛት ለሚፈልጉ ደምበኞቹ በተለምዶ ቄራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቅጥር ግቢው ዙሪያ ባሉ የስጋ መሸጫ ሱቆች የበግ ስጋ በኪሎ በ600 ብር፣ የፍየል በ620 ብር እና የበሬ ስጋ በኪሎ በ700 እንዳቀረበ ተናግረዋል።


በሌላ በኩል ባለፉት 6 ወራት ህገ ወጥ እርድንና የስጋ ዝውውር ለመቆጣጠር በተሰራ ሥራ 6 ሺህ 620 ኪሎ ግራም የተበከለ ስጋ እንደተወገደ አቶ አታክልቲ አስረድተዋል።


በዚህ ህገወጥ ተግባር ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉና ጤናማነቱ ያልተረጋገጠ ስጋን ለማህበረሰቡ ሲሸጡ የተደረሰባቸው 150 ልኳንዳ ቤቶች ላይ ከማሸግ እስከ ገንዘብ ቅጣት የደረሰ እርምጃ እንደተወሰደም ጠቅሰዋል።


ድርጅቱ በመደበኛነት ከበዓላት ውጭ ባሉት ቀናት በየቀኑ የ3ሺህ እንሰሳት እርድ እንደሚከውን ተናግሯል።

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page