top of page

ታህሳስ 25፣2017 - በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ መከሰቱን ዞኑ ለሸገር ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Jan 3
  • 1 min read

በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ መከሰቱን ዞኑ ለሸገር ተናገረ፡፡


ዛሬ ማለዳ 3 ሰዓት አካባቢ በዞኑ ዱለሳ ወረዳ ሰጋንቶ ቀበሌ ላይ ነው እሳተ ገሞራው የፈነዳው ተብሏል፡፡


በተጠቀሰው አካባቢ ያሉ ተራራ ላይ አዳዲስ ፍንዳታዎች መኖራቸውን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዶ አሊ ነግረውናል፡፡


በፍንዳታው ከሚወጣ ጭስ ጋር አብሮ ጭቃ እየተትጎለጎለ ወደ ላይ ይፈናጠራል ያሉት አቶ አብዶ ጭቃው ሰውነት ላይ ካረፈ በጣም ያቃጥላል ይላሉ፡፡


ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ዶፈን ተራራ ላይ የተለያዩ የእሳተ ጎመራ ፍንዳታዎች እንደተከሰቱ የተናገሩት የዞኑ አስተዳደሪ እሳቸው የሰሙት ግን ከማለዳው 3 ሰዓት ላይ የተከሰውን እንደሆነ ነግረውናል፡፡


በአካባቢው ምን እየተካሄደ ነው? ሁኔታው ወዴትስ ያመራል? የሚለውን በተመለከተ የጠየቅነው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ተቋም ስለፈነዳው እሳተ ገሞራ ለጊዜው መረጃ የለኝም ብሏል፡፡

ree

የፀጥታ ችግሮች እና በመሬት መንቀጥቀጥ በመመዝገቢያ ጣቢያዎቸ ላይ የሚፈፀም ስርቆት በተፈለገው መጠን ሁኔታውን ለመከታተል እንቅፋት ሆኖብኛል ሲል ነግሮናል፡፡


በተጠቀሰው አካባቢ አቅራቢያ ከአዋሽ ፈንታሌ የሚነሳ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ በተደጋጋሚ እየተሰማ መሆኑ ይታወቃል፡፡


እስካሁን ከፍተኛ የተባለው በሬክተር ስኬል መለኪያ 5.1 ሆኖ ተመዝግቧል፡፡


ወንድሙ ሀይሉ

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page