top of page

ታህሳስ 24፣2017 - ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ማሻሽያ ማድረጓ ለኢትዮጵያ ባንኮችን ስኬት ወይስ እንቅፋት ሆናቸው?

  • sheger1021fm
  • Jan 2
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ማሻሽያ ካደረገች ስድስት ወር ሞላት፡፡


ያለፉት ስድስት ወራት ለኢትዮጵያ ባንኮችን ስኬት ወይስ እንቅፋት? የውጭ ምንዛሪ ማሻሽያው በባንኮች ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ ምንድነው?


በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንቲትዩት የባንክ እና ፋይናንስ ተመራማሪ የሆኑት የተወልደ ግርማ(ዶ/ር) ጥናት ለእነዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣል፡፡


ተወልደ ግርማ የውጭ ምንዛሪ ገበያ መር እንዲሆን ሲወሰን ሁሌም ቢሆን በባንኮች ላይ ከፍተኛ ጫና እንደሚሳድር ነግረውናል፡፡

ree

በውጭ ገንዘብ ተበድረው የነበሩ ባንኮች ከማሻሽያው በፊት ይከፍሉት የነበረውን እዳ በሁለት እና በሶስት እጥፍ ከማሻሽያው በኋላ እንዲከፍሉ አድርጓል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ማሻሽያው በባንኮች የማይመለስ ብድር ላይም ከፍተኛ ጫና ማሳደሩንም ተመራማሪው በጥናታቸው ተመልክቻለው ይላሉ፡፡


በዚህም በውጭ ገንዘብ የተወሰዱ ብድሮች እስካሁን በሚፈለገው ደረጃ ለባንኮች እንዳልተመለሰም ዶ/ር ተወልደ ግርማ አስረድተዋል፡፡


ተመራማሪው፤ የውጭ ምንዛሪ ማሻሽያው የሀገሪቱ ባንኮች የባህሪይ ለውጥ እንዲደርጉ ማስገደዱንም አስረድተዋል፡፡


ለምሳሌም ባንኮች የውጭ ሀገር ገንዘቦችን ዋጋ በመመልከት የብድር አሰጣጣቸውን ወደ ውጭ ለሚላኩ ምርቶች እንዲያዘነብሉ አድርጓል ብለዋል፡፡


ሌላው የባህሪይ ለውጥ ከማሻሽያው ወዲህ ዜጎች የሀገራቸው ገንዘብ የመግዛት አቅሙ በመዳከሙ ምክንያት በባንክ ያላቸውን ገንዘብ ወደ ውጭ ምንዛሪ እንዲለውጡ እና እንዲስቀምጡ አድርጓል ብለዋል፡፡


በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንቲትዩት የባንክ እና ፋይናንስ ተመራማሪ የሆኑት ተወልደ ግርማ(ዶ/ር) ከማሻሽያው በፊት ያልነበሩ ሶስት አዳዲስ ለውጦች መኖራቸውን በጥናታቸው ለይተናል ይላሉ፡፡


እነሱም ከዚህ በፊት ያልነበሩ ማለትም በባንኮች መካከል ያለው ውጭ ምንዛሪ ግብይት ጭምሯል፣ የሀገሪቱ ገንዘብ ክምችት ጭማሪ እና የውጪ ምንዛሪ ቢሮዎች መከፈት ናቸው ሲሉ አስረድተዋል፡፡


አሁን አገሪቱ ባንኮች ላለባቸው ተጽዕኖ መውጫ መንገድ ይሆናል ያሉንት ምክረ ሀሳቡም ነግረውናል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd


📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s


📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il


Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page