top of page

ታህሳስ 23፣2017 - አዋጭ የተሰኘው የብደርና ቁጠባ ተቋም በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ አባላቱ በነፃ የገና ባዛር አሰናድቷል

  • sheger1021fm
  • Jan 1
  • 1 min read

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ስራ ማህበር በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ አባላቱ በነፃ የገና ባዛር አሰናድቷል፡፡


ከተቋሙ ብድር ወስደው የተለያየ ምርት እያመረቱ ያሉ ከ70 በላይ ለሆኑ አባላቱ በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ ሾላ የገበያ ማዕከል ውስጥ ባዛር አሰናድቷል፡፡


አዋጭ ቁጠባን ከአባላቱ በማሰባሰብ ለ42,000 አባላቱ ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ሰጥቶ እያንቀሳቀሰ እንደሆነ የተናገሩት የህብረት ስራ ማህበሩ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ዘሪሁን ሸለመ ናቸው፡፡

ree

ይህ ባዛር አዋጭ ለአባላቱ ብድር መስጠት ብቻ ሳይሆን የተሰጠው ብድር ከምን እንደደረሰ ማሳያ ነው ያሉት ደግሞ የአዋጭ የስራ አመራር ቦርድ ዋና ስብሰባ አቶ መስፍን ገብረስላሴ ናቸው፡፡


ከታህሳስ 22 እስከ ታህሳስ 28 2017 ዓ.ም በሚቆየው የገና ባዛር ተሳታፊ አባላት የራሳቸው ምርት እንዲሁም ሌሎች ግብአቶችን ይዘው በመቅረብ ለሸማቾች ምቹ ገበያን ይፈጥራሉ ተብሏል፡፡


በባዛሩ ላይ የሀገር ባህል ልብሶች፣ የቤት እቃዎች፣ የቆዳ ውጤቶችና የመሳሰሉት ይገኙበታል ተብሏል፡፡



ማርታ በቀለ

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page