top of page

በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል።

  • 2 hours ago
  • 1 min read

ሚያዝያ 20/2018

 

በኢትዮጵያ በፋይናንስ ተቋሞች የተከፈተ የቁጠባ ሂሳብ ቁጥር ከ176 ሚሊየን በላይ ደርሷል። 

 

ከዚህ የባንክ ሂሳብ 97 በመቶው ግን ከ100 ሺህ ብር በታች ገንዘብ የተቀመጠበት መሆኑ ተነግሯል። 

 

በኢትዮጵያ የፋይናንስ ተቋሞች በኪሳራ ምክንያት ቢዘጉ ገንዘቡን የቆጠበው ሰው ያስቀመጠውን እንዳያጣ ለመካስ በሚል የተቋቋመው የኢትዮጵያ የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ ስራ ከጀመረ ሶስት ዓመት ሆኖታል። 

 

ፈንዱ በዚህ ጊዜ ከባንኮችና ሌሎች የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የሰበሰበው የአረቦን ገንዘብ ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱ ተነግሯል። 

 

ከጠቅላላ አረቦኑ አብዛኛው ወይም 10.41 ቢሊዮን ብሩ ከግል ባንኮች የተሰበሰበ እንደሆነ ፈንዱ ከላከልን መረጃ ላይ ተመልክተናል።

 

 9.96 ቢሊዮን ብሩ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ ቀሪው 0.24 ቢሊየን ብር ከማክሮ ፋይናንስ ተቋማት የተሰበሰበ ነው ብሏል፡፡

 

በኢትዮጵያ ያሉ 31 የንግድ ባንኮችና 64 የማይክሮ ፋይናንስ ተቋሞች ከአማካይ ቁጠባቸው 0.3 በመቶውን በአረቦን መልክ ለፈንዱ ይከፍላሉ። 

 

ፈንዱም ባንኮች እና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት በኪሳራ ቢዘጉ የቆጣቢውን እስከ 100 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ ይመልሳል። 

 

ግን ከፈንዱ ለቆጣቢዎች የሚመለሰው የገንዘብ ጣራ ለምን 100ሺህ ብር ብቻ ሆነ የሚል ጥያቄ ሲነሳ ይሰማል። 

 

ይህንን እና ሌሎች የሚነሱ ጥያቄዎችን ለተቋሙ የስራ ሀላፊ አንስተናል። 

 

 

ቴዎድሮስ ወርቁ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page