top of page

በታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ከፍተኛ ትችት ከባለሞያዎች ቀረበበት።

  • May 20
  • 2 min read

ግንቦት 12/2018


በታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ግብር ከፋይዮች አንዴ የተወሰነባቸውን ግብር መጠን ተገቢ እንዳልሆነ የሚያስረዳ አዲስ ማስረጃ እንዳያቀርቡ መከልከሉ ከፍተኛ ትችት ከባለሞያዎች ቀረበበት።


የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ አዲስ ማስረጃ ማቅረብ ሙሉ በሙሉ አልተከለከልም፣ የሚፈቀድብት ሁኔታ አለ ብሏል፡፡


ረቂቁ በአንድ ግብር ዘመን ከሁለት ጊዜ በላይ ቅጣት የተጣለበት የግብር ከፋይ ድርጅት ስራ አስኪያጅ፣ የፋይናንስ ሀላፊ ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎችን በወንጀል ህግ እንዲጠየቁ የሚያደርግ ነው።

በረቂቅ አዋጁ ላይ ትችቱ የቀረበው የገንዘብ ሚኒስቴር ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ባካሄደው የባለድርሻ አካላት ወይይት ላይ ነው።


በውይይቱ ላይ የተቋማት የስራ ሃላፊዎች፣ የድርጅት ተወካዮች፣ የግብር የህግ አዋቂዎች እና ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።


ሽሂር ሸሞሎ የተባሉ ተሳታፊ በግብር አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በአዲስ የተካተተውን "የኢዲስ ማስረጃ" ክልከላን አላስፈላጊ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡


በረቂቁ መሰረት “አዲስ ማስረጃ” ማለት የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ በታክስ ከፋዩ የሚቀርብ አዲስ ሰነድ፤ መረጃ፤ ማስረጃ እና ፍሬነገር መሆኑ ተደንግጓል፡፡


በዚህም መሰረት በመጀመሪያው የታክስ አወሳሰን ሂደት ለታክስ ባለስልጣኑ ያልቀረበ፤ለታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው ትክክለኛነት አግባብነት ያለው እና የታክስ መጠን ወይም በታክስ ከፋዩ ግዴታ ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያስከትል ነው ይላል፡፡


ይህም ቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም የውሳኔ ማስተካከያ ጥያቄን የሚያቀርብ ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ወቅት ካቀረበው የተለየ አዲስ ማስረጃን ማቅረብ አይችልም፡፡


ከላይ የተዘረዘረው እንደተጠበቀ ሆኖ በተለየ ሁኔታ አዲስ ማስረጃ የሚፈቅደበትን ሁኔታ ረቂቁ ሲዘረዝር አዲስ ማስረጃ በቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም ስህተትን ለማረም በሚቀርብበት ወቅት ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው መንገድም ዘርዝሯል፡፡


በዚህም ሰነዱ ያለመታየቱ በግብር ከፍዩ የታክስ እዳ ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል ከሆነ፤ ሰነዱን ታክስ ከፋዩ ያገኘው የግብር ውሳኔ በከተሰጠ በኋላ ከሆነ ወይም ሰነዱ ያልቀረበው አቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሆነ እንደሆነ ደንግጓል፡፡


ታክስ ከፋዩ በታክስ እዳው ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል አዲስ ማስረጃ ያቀረበ ከሆነ ደግሞ በታክስ ሕጉ መሠረት ሰነዱ በታክስ አወሳሰን ወቅት አስቀድሞ ባለመቅረቡ ምክንያት ሊከፈል ይገባ የነበረውን የታክስ ዕዳ 20 በመቶ ቅጣት ይከፍላል ይላል፡፡


ታዲያ ይህ የድንጋጌ ክፍል ከበለሞያዎች ከፍተኛ ተችት ቀርቦበታል፡፡


አቶ ሽሂር ሸሞሎ ይህ የሀግ ከፍል አገሪቱ ካለችበት እውነታ ጋር አብሮ ስለማይሄድ ቢወጣ ሲሉ መክረዋል፡፡


አቶ ሻሂር የታክስ ስርዓቱን "የመጨረሻ ውስብስብ ነው" የሚያደርገው ሲሉ ተናግረዋል፡፡


የታክስ ባለሥልጣን ምን ኦዲት እንደሚያደርግ አይታወቅም ያሉት ተሳታፊው ይህ ድንጋጌ የአገሪቱ የግብር ስርዓት የሚረብሽ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡


ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ በኢዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል መምህር እና ጠበቃ አቶ አስቻለው አሻግሬ ረቂቁ "ጭካኔ የተሞላበት ነው" ሲሉ ተችተዋል፡፡


በረቂቁ አዲስ ማስረጃን በተመለከተ የተደነገገው "በለፉት 40 ፣ 50 ዓመታት ታይቶ የማይታወቅ ወደኋላ የሚመልስ ነው " ሲሉ ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡



ለቀረበው ትችት እና አስተያት ምላሽ የሰጡት በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት አቶ ዋሲሁነ አባተ በበኩላቸው አዲስ ማስረጃ ማቅረብ ሙሉ በሙሉ እንዳልተከለከለ አስረድተው የሚፈቀድብት ሁኔታ መዘርዘሩን ጠቅሰዋል፡፡


ረቂቅ ህጉ እያለ ያለው የኦዲት አሰራሩ ህግን ይከተል ነው ሲሉ አቶ ዋሲሁን አክለዋል፡፡


የታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በንባብ ለታሳታፊው ያቀረቡት አማካሪው ደረሰኝ ባለመስጠት የጣለው አስተዳደራዊ ቅጣት ከነበረበት 50 ሺህ ወደ 100 ሺህ ማደጉን ተናግረዋል፡፡


በአንድ ግብር ዘመን ከሁለት ጊዜ በላይ ቅጣት የተጣለበት የግብር ከፋይ ድርጅት ስራ አስኪያጅ፣ የፋይናንስ ሃላፊ ጨምሮ ሌሎች ተሳታፊዎችን በወንጀል ህግ እንዲጠየቁ የሚደርግ ነው ብለዋል።


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….


ያሬድ እንዳሻው



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች?

ሰኔ 15/2018 ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች? በ2025 ስራውን በ700 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ አደርጋለሁ ብትልም እዛ ማድረስ ግን አልቻለችም ታዲያ ከ አምስት አመት በኋላ እንደቃሏ

 
 
 
የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡

ሰኔ 15/2018 የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡ በእዚሁ ምክንያት የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ግማሽ ያህል ሰራተኞቹን መቀነሱን እና የሰረዘው ፕሮጅክትም መኖሩን መናገ

 
 
 
በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡

ሰኔ 15/2018 በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡ የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት በተለያዩ ሶስት ፋብሪካዎች ለአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚሆኑ ከ69 ቶን በላይ የመጠቀሚያ ጊዜ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page