ሰኔ 26 2017 - ''ኢትዮጵያ በመጪው ዓመት ጋዝ አምርታ ለአለም ገበያ እንደምታቀርብ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ተናገሩ
- sheger1021fm
- Jul 3
- 1 min read
ኢትዮጵያ በመጪው ዓመት ጋዝ አምርታ ለአለም ገበያ እንደምታቀርብ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡
የጋዝ ማስተላለፊያ መሰረተ ልማቱም በሶማሌ ክልል ተገንብቶ መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማው ተናግረዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በመጪው ዓመት መጀመሪያም ለገበያ ይቀርባል ሲሉ የተናገሩት ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ተገኝተው ከእንደራሴዎቹ ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡ ጊዜ ነው፡፡
በተጨማሪም ከናይጀርያው ባለሀብት አሊኮ ዳንጎቴ ጋር በተደረገ ስምምነት በጥቂት ወራት ውስጥ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ መገንባት ትጀምራለችም ብለዋል፡፡
ፋብሪካው በሶስት ዓመት ከመንፈቅ ተጠናቅቆ ይመረቃል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የወርቅ ምርት ከአምናው በብዙ እጥፍ አድርጎ ዘንድሮ 3.5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቶበታል ብለዋል፡፡
አምና የተመረተው እና ለአለም ገበያ የተላከው ወርቅ 4 ቶን ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘንድሮ 37 ቶን በመላክ ነው ከፍተኛ የተባለ የውጪ ምንዛሪ የተገኘው ብለዋል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s
📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6








