top of page

ሰኔ 18 2017 - በምርት እና ፍላጎት አለመጣጣም ምክንያት አንድ እንቁላል እስከ 25 ብር እንዲሸጥ እድል ፈጥሯል ተብሏል

  • sheger1021fm
  • Jun 25
  • 1 min read

በዶሮ እርባታ ላይ የተሰማሩ ትናንሽ አርቢሮች ከዘርፉ መውጣታቸው ለእንቁላል መወደድ ምክንያት ሆኗል ተባለ።


አርቢዎቹ ከዘርፉ እንዲወጡ ያስገደዳቸውም የመኖ ዋጋ ውድነት እንደሆነ ሰምተናል።


መኖ አቅራቢ ፋብሪካዎችም ቢሆኑ በጥሬ እቃ እጥረት እና መወደድ ምክንያት እየተቸገሩ መሆኑን ሰምተናል።


በዚህ እና በሌሎች ተደራራቢ ምክንያቶች የእንቁላል መኖ ዋጋ ከፍ ማለቱን ተነግሯል።


አንድ ኩንታል የእንቁላል ጣይ የዶሮ መኖ ከሁለት ወር በፊት ሲሸጥ ከነበረው 4,800 ብር አሁን 5,800 ብር እየተሸጠ መሆኑን ሰምተናል፡፡


በተለይ አቅም የሌላቸው ትናንሽ አርቢዎች እየተቸገሩ በመምጣታቸው ከገበያው ለመውጣት ይገደዳሉ የተባለ ሲሆን በምርት እና ፍላጎት አለመጣጣም ምክንያት አንድ እንቁላል እስከ 25 ብር እንዲሸጥ እድል ፈጥሯል ተብሏል።


በሌላ በኩል ደግሞ መኖ አቅራቢ ፋብሪካዎችም በብዙ ይፈተናሉ የተባለ ሲሆን ለመኖ ማቀነባበሪያ የሚውሉ ግብዓቶችን አለማግኘት ዋነኛ ችግራቸው እንደሆነ ተነግሯል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ፋሲካ ሙሉወርቅ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page