ማስረጃ ሳይቀርብ፣ እንዲሁም መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ በተፈፀመ ክፍያ የተለያዩ መ/ቤቶች በቢሊዮን የሚቆጠብ ብር ያላግባብ ወጪ ማድረጋቸው ተረጋገጠ፡፡
- 5 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 11/2018
የሒሳብ አያያዝ መመሪያዎችን በመጣስ ማስረጃ ሳይቀርብ፣ እንዲሁም መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ በተፈፀመ ክፍያ የተለያዩ መ/ቤቶች በቢሊዮን የሚቆጠብ ብር ያላግባብ ወጪ ማድረጋቸው ተረጋገጠ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የ2017 የሒሳብ ምርመራ ሪፖርት እንደሚያሳየው የተሟላ የወጪ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጭ ተመዝግቦ የተገኘ ከ1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ማስረጃ ሳይቀርብ ወጪ የተደረገ 35.8 ሚሊዮን ፣ ደንብና መመሪያ ያልተከተለ ወጭ ደግሞ 57.8 ሚሊዮን ብር እና በብጫና ድጋሚ ያላግባብ በተፈፀመ ክፍያ 280.6 ሚሊዮን ብር ያለአግባብ ከመስሪያ ቤቶች ወጪ ተደርጎ መገኘቱን ጠቅሷል፡፡

መመሪያ ተጥሶ መከፈል ካለበት በብልጫና ድጋሚ ያላግባብ ክፍያ ፈፅመዋል ከተባሉት መካከል፡-
ጤና ሚኒስቴር 231.1 ሚሊዮን ብር፣
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን 23 ሚሊዮን ብር፣
የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ፣
የቃሊቲ ጉምሩክ ቅፅ/ቤት 2.4 ሚሊዮን ብር፣ እና ጅማ ዩኒቨርሲቲ 2.1 ሚሊዮን ብር ወጪ ያደረጉ መሆኑ በሒሳብ ምርመራው ተረጋግጧል ተብሏል፡፡
እንዲሁም የተሟላ የወጭ ማስረጃ ሳይቀርብ በወጭ ተመዝግቦ ከተገኘው 1.1 ቢሊዮን ብር በላይ መካከል፡-
የሞያሌ ጉምሩክ 25.4 ሚሊዮን ብር፣
የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት 23.4 ሚሊዮን ፣
የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት 7.5 ሚሊዮን ፣
የማዕድን ልማት ኢንስቲትዩት 6.6 ሚሊዮን፣
የማዕድን ሚኒስቴር ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እና
የባህር ዳር የጉምሩክ 4.7 ሚሊዮን ከፍተኛውን ድርሻ የያዙ ናቸው ተብሏል፡፡
ያለበቂ ማስረጃ ክፍያ መፈፀምን ጨምሮ ደንብና መመሪያ ተጥሶ የሚፈፀሙ ክፍያዎች ተጠያቂነትን ያስከትላሉ ያለው የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ገንዘቡ ተመላሽ እንዲደረግ አሳስቧል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን




Comments