top of page

መስከረም 30፣2017 - ህሙማን የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ መንግስት ጤና ተቋማት ሲሄድ ስድብን ጭምሮ የተለያ ውክቢያዎች እንደሚደርስባቸው ተነገረ

  • Oct 10, 2024
  • 1 min read

ህሙማን የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ መንግስት ጤና ተቋማት ሲሄድ ስድብን ጭምሮ የተለያ ውክቢያዎች እንደሚደርስባቸው ተነገረ፡፡


ይህ የተነገረው የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ላይ ባደረገው ወይይት ነው፡፡


የጤና አገልግሎት አስተዳደር እና ቁጥጥር ረቂቅ አዋጅ ህሙማንን ከእንግልት እና ከማመነጫጨቅ የሚጠብቅ እንዲሆን ተጠይቋል፡፡


ነዋሪዎች የህክምና እርዳታ ለማግኘት ወደ መንግስት የጤና ተቋማት ሲሄዱ ክብራቸውን በጠበቀ መንገድ እንዲስተናገዱ የእንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ጠይቀዋል፡፡


የጤና ተቋማት ህክምና እርዳት ሲሰጡ የታካሚውን ክብር እንዲጠብቁ በአዋጅ ሊካተት ይገባል ሲሉ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት አቶ አስቻለ አላምሬ ተናግረዋል፡፡


የጤና አገልግሎት የስነምግባር መርሆች ላይም ቅንነት እና ታማኝነት በረቂቅ አዋጁ እንዲካተት ተጠይቋል፡፡

ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡

ሐምሌ 21 2018 በአዲስ አበባ በተጠናቀቀው በበጀት አመት 117 ሺህ ህፃናት ተወልደው የልደት ማረጋገጫ ሰጥቻቸዋለው ሲል የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተናገረ፡፡ ይህም ህፃናቱ ተወልደው በ90 ቀናት ውስጥ የተመዘገቡ ናቸው ሲሉ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ዮሴፍ ንጉሴ አስረድተዋል፡፡ ዘግይተው

 
 
 
ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡

ሐምሌ 21 2018 ከህዳሴ ግድብ ከ11 ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ዓሣ ተመረተ፡፡ የዓሣ ምርቱ ወደ መሃል ሃገር እየተጫነ ለአዲስ አበባ ገበያ እየቀረበ ነውም ተብሏል፡፡ ታላቁ የህዳሴ ግድብ መገንባቱን ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሰው ሰራሽ ሃይቅ በኢትዮጵያ ትልቁና ከ70 በላይ ደሴቶች ያሉት የውሃ አካል ነው፡፡ ከቅርብ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page