top of page

መስከረም 14 2018 -ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብን ሀምሳ ሀምሳ ሆነው መጎብኘት ለሚፈልጉ ጉብኝት ተጀምሯል

  • sheger1021fm
  • Sep 24
  • 1 min read
ree

ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ተመርቆም አሁን ደግሞ ለጉብኝት ክፍት የተደረገው የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ መገኛው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉባ ከተማ ነው፡፡


ለመሆኑ ግድቡ የሚገኝበት የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ጎብኚዎችን ለማስተናገድ ምን አዘጋጅቷል?


በሳምንት ሁለቴ በረራ እንዳለ የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ መናገራቸው ይታወሳል፡፡


በዚህም ለህዳሴው ጉብኝት የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ምን ያህል ዝግጁ ናቸው? ስንል የክልሉን የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የዕቅድ እና ዝግጅት ክፍል ዳይሬክተር አቶ ታምራት ሙሊሳን ጠይቀናል፡፡


የመሰረተ ልማቶች ምን ያህል የተሟሉ እንደሆኑና የፀጥታ ስጋት አሁን ላይ ምን ይመስላል? ስንል ዳይሬክተሩን ጠይቀናል፡፡


የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው ለጉብኚዎች መሟላት አለባቸው ያሉትን እና መሰረተ ልማቶች እንዲሁም እየተሰሩ ስላሉ ስራዎች ተናግረዋል፡፡


የህዳሴው ግድብ ለቱሪዝሙ ዘርፍ የጎል አስተዋጽኦ እንዳለውም አስረድተዋል፡፡


ማርታ በቀለ


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…👇👇👇👇👇👇



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page