top of page

መስከረም 13 2018 - የተገኙ 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ እንዲሰረዝ ጥያቄ ቀረበ።

  • sheger1021fm
  • Sep 23
  • 1 min read

የመንግስትን ጥቅም ለማሳጣት የሚያስችል ግድፈት ፈፅመው የተገኙ 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሙያ ፈቃድ እንዲሰረዝ ጥያቄ ቀረበ።


ይህንን ያለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ነው።


ቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የ13 ግብር ከፋዮች መዝገብ በማዘጋጀት ካቀረቡ ባለሙያዎች መካከል ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የመንግስትን ጥቅም ለማሳጣት የሚያስችል ግድፈት ፈፅመው ተገኝተዋል በተባሉ 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች ላይ ነው የሙያ ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ጥያቄ የቀረበው ተብሏል።

ree

ቢሮው ይኸን ጥያቄውን ያቀረበው በታክስ አስተደደር አዋጅ መሰረት ለኢትዮጲያ የሂሳብና ኦዲት ቦርድ መሆኑ ተነግሯል።


በቢሮው የሙያ ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ጥያቄ የቀረበባቸው 10 የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች በቦርዱ የሙያ ፈቃድ የተሰጣቸው መሆናቸውንም አሳውቋል፡፡


የከተማ አስተዳደሩ ግብር ከፋዮች ቢሮው የሙያ ፈቃድ ስረዛ በተጠየቀባቸው የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች ተዘጋጅተው የሚቀርቡ የሂሳብ መዝገቦችን አልቀበልም ብሏል።


የስም ዝርዝራቸውን ከቦርዱ በመጠየቅ የሙያ ስነ ምግባሩን ጠብቀው በሚሰሩ የሂሳብ ባለሙያዎችና ኦዲተሮች የሂሳብ መዝገቡን በማሰራት እንዲያቀርብ አሳስቧል፡፡


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page