top of page

ሐምሌ 16 2017 - ከ10 ዓመት በፊት 1.7 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት ጉዳቱ ተጠንቶ ተለይቷል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Jul 23
  • 1 min read

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው በቱርኩ ያፒ መርከዚ ተቋራጭ ከ10 ዓመት በፊት 1.7 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት ጉዳቱ ተጠንቶ ተለይቷል ተባለ።


በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ዝርፊያ ተፈፅሞበታል የተባለው፤ ስራውም ተቋርጦ የቆየው ይህ ፕሮጀክት እንደገና ለመቀጠልም ስራ መጀመሩ ተሰምቷል።


ባቡሩ ከጦርነት እና ግጭት ባለፈ በተፈጥሮ፤ መሬት መንቀጥቀጥ ጭምር የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ጉዳት እንደደረሰበት ተረድተናል።

ree

የዚህን ፕሮጀክት ዳግም ጀምሮ ለማጠናቀቅ ጉዳቱ እንደተለየና በእቅድ እንደተያዘ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው ነግረውናል።


አዋሽ ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ንጣፍ መስመር ፕሮጀክት 375 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ነው።


መስመሩ ሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያን ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኝ ነው።


የአፋር፣ የአማራና የትግራይ ክልሎች ደግሞ ይኸው የባቡር ንጣፍ መስመር የሚያልፍባቸው ናቸው።


ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው ይህ ባቡር በሰዓት 120 ኪሎ ሜትር እንዲወረወር ተደርጎ ዲዛይን የተደረገለት ነበር።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page