top of page

ሐምሌ 10 2017 - የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅና የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ፀደቀ

  • sheger1021fm
  • Jul 17
  • 1 min read

የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ እና የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቦ ፀደቀ፡፡


ምክር ቤቱ 4ኛ የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባውን ዛሬ አድርጓል፡፡


በዛሬው ስብሰባውበኢትዮጵያ #የምርጫ_የፖለቲከ_ፓርቲዎች_ምዝገባና_የሥነ_ምግባር አዋጅን በማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፣ የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን እንዲሁም የስታርታፕ ረቂቅ አዋጅን በተመለከተ የሚቀርቡ ሪፖርትና የውሳኔ ሀ ቦችን መርምሮ ለማፅደቅ ቀጠሮ ይዞ ነበር፡፡


በዚህ መሰረት ብዙ ክርክርና ሲደረግበት የነበረው #የገቢ_ግብር አዋጅ ማሻሻያ አዋጅ በሁለት ተቃውሞና በ4 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡


በ26 አንቀፆች ላይ ማሻሻያ ተደረገበት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅን ቁጥር 1394/2017 ሆኖ በምክር ቤቱ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page