top of page

ህዳር 6፣ 2017 - አክሱም ሰላም ከወረደ ሁለት ዓመታት ቢያስቆጥርም፤ የሚታሰበውን ያህል ቱሪስቶችን ሊጎበኟት አለመቻላቸው ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Nov 15, 2024
  • 1 min read

አክሱም ሰላም ከወረደ ሁለት ዓመታት ቢያስቆጥርም፤ የሚታሰበውን ያህል ቱሪስቶችን ሊጎበኟት አለመቻላቸው ተነገረ፡፡


የበርካታ ጥንታዊ ቅርስ መገኛ የሆነችው #አክሱም_ከተማ ከሰሜኑ ጦርነት ቁዘማ መላቀቋን ያነጋገርናቸው የከተማው ነዋሪዎች ያስረዳሉ፡፡


ባለፉት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ በነበረው #ጦርነት ምክንያት የቱሪዝም እንቅስቃሴ አክሱም ከተማ ውስጥ ተቋርጦ እንደነበር የነገሩን እነዚህ ነዋሪዎች አሁንም አክሱም ውስጥ ሰላም ቢሰፍንም በሚፈለገው ጎብኚ እየመጣ አለመሆኑን ይናገራሉ፡፡


አቶ ሰለሞን ተክላይ በሆቴል ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብት ሲሆኑ አክሱም ከተማ ሰላም ሆና ቱሪስቶችን እየጠበቀች ቢሆንም፤ እስካሁን በክልሉና በፌደራል መንግስት በኩል ተገቢው የማስተዋወቅ ስራ ባለመሰራቱ የቱሪስቶች ቁጥር ሊጨምር እንዳልቻለ ነግረውናል፡፡

ree

በአስጎብኚነት ስራ የተሰማራው አቶ ሰለሞን ገብረፃድቅ በበኩላቸው አክሱም ከተማ እንግዶችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቷን ካጠናቀቀች ቆየት ብሏል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ነገር ግን #ቱሪስቶች አክሱም ሰላም መሆኗን ስለማያውቁ እንቅስቃሴው ቀዝቃዛ መሆኑን ይናገራሉ፡፡


የቱሪዝም ሚኒስቴር የማስታወቂያ ዴስክ ኃላፊ አቶ ንጉሴ እሸቱ፤ በሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን የቱሪስት ስፍራዎች ለማስተዋወቅ እየሞከርን ነው ብለዋል፡፡


ነገር ግን የውጪ ሀገራት ኤምባሴዎች የጉዞ እቀባ መጣላቸው የውጪ ሀገራት ጎብኚዎች እንዳይገኙ ችግር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡


በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


📌YouTube: https://t.ly/9uH-g


 

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page