top of page

ህዳር 3፣ 2017 - ‘’በትጥቅ አመጽ ይንቀሳቀሱ ከነበሩት ጋር ስምምነት ፈጥሬ በጋራ እየሰራን ነው’’ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል

  • sheger1021fm
  • Nov 12, 2024
  • 1 min read

‘’በትጥቅ አመጽ ይንቀሳቀሱ ከነበሩት ጋር ስምምነት ፈጥሬ በጋራ እየሰራን ነው’’ ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተናገረ፡፡


ወደ ሰላም የተመለሱ ታጣቂዎችን በካቢኒ አባልነትን ጨምሮ በተለያዩ የስራ መስኮች በመሳተፍ እየሰሩ ይገኛሉ ተብሏል፡፡


በክልሉ በአሁን ሰዓት ምንም አይነት የሚያሰጋ የጸጥታ ችግር የለም ሲል ክልሉ ለሸገር ራዲዮ ነግሯል፡፡


መንግስትን በመቃወም ጫካ ገብተው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የተለያዩ ቡድኖች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ትጥቅ ፈትተዋል ተብሏል፡፡

ree

ይህንን ለሸገር የነገሩት፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሰላም ግንባታና ጸጥታ ቢሮ የሰላም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ጸሀይ ጉዮ ናቸው፡፡


በክልሉ ቀድሞ የነበረው የጸጥታ ችግር ጥሎት ያለፈው ክፍተቶችን ለማስተካከል እየተሰራ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡


ይሁንና ወደ ሰላም የተመሱት ለመደገፍ ክልሉ የፋይናንስ እጥረት እንደገጠመው አቶ ጸሀይ ጠቅሰዋል፡፡


''ይህንን ክፍተት ለማስተካከልም እየተሰራ ነው'' ብለዋል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን

Recent Posts

See All
ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ 

ታህሳስ 11/2018   ወደ ቀድሞ ቀያቸው ሄደው እንደገና ወደ ደብረብርሃን የተመለሱ ተፈናቃዮች መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡   የአማራ ክልል የአደጋ ስጋት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ መልስ ለመስጠት አልፈቀደም።   ከመንግስት የሚቀርበውን ድጋፍ ለተፈናቃዮች የሚያከፋፍለውና ሌሎች ስራዎችን የሚሰራው በመንግስት የተቋቋመ ኮሚ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page