top of page

ጥቅምት 12፣2016- በሱዳን ጦርነት የተነሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀን በአማካይ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ለማውጣት ተገዶ እንደነበረ ተሰማ


በሱዳን በተቀሰቀሰው ጦርነት የተነሳ ሀገሪቱ የአየር ክልሏን ለበረራ ዝግ በማድረጓ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለይ ወደ ምዕራብ አፍሪካ ሀገሮች የሚያደርገውን በረራ በኬንያ እና በዩጋንዳ ለማድረግ በመገደዱ በቀን በአማካይ ከ6 ሚሊዮን ብር ለማውጣት ተገዶ እንደነበረ ተሰማ፡፡


በአሁኑ ሰዓት ግን የደቡብ ሱዳንን የላይኛውን የአየር ክልል አማራጭ የአደጋ ጊዜ የበረራ መስመርነት አየር መንገድ እየተጠቀመ እንደሆነ ሰምተናል፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በሱዳን ጦርነት የተነሳ ሀገሪቱ የአየር ክልሏን ለበረራ ዝግ በማድረጉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀገር ውጪ ለሚያደርገው በረራ ባያፍታቱትም ብዙ ችግር እንዳጋጠመው ጠቅሰዋል፡፡


የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአየር ትራፊክ ማኔጅመንት ዳይሬክተር አቶ ዮሀንስ አበራ የሱዳን የአየር ክልል መዘጋት አየር ክልሉን ለሚጠቀሙ አየር መንገዶች ከፍተኛ ወጪ መደረጉን አስታውሰዋል፡፡


በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀን በአማካይ 94,000 ሊትር ነዳጅ ወይንም በገንዘብ ሲሰላ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲያወጣ ተገዶ ነበር ብለዋል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2024 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page