top of page

ነሐሴ 2፣2015 - የኒጀር የመንግስት ገልባጮች ለሀገሪቱ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰየሙ

በገልባጮቹ በጠቅላይ ሚኒስትር የተሾሙት ዓሊ ማሐማን ላሚን ዛይን እንደሆኑ ፒፕልስ ጋዜት ፅፏል፡፡


ላሚን ዛይን በተገለበጠው መንግስት የምጣኔ ሐብታዊ ጉዳዮች ሚኒስትር እንደነበሩ ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኒጀር ፕሬዘዳንታዊ ዘብ የጦር ክፍል ባልደረቦች የፕሬዘዳንት ሞሐመድ ባዙምን መንግስት ከገለበጡት 2 ሳምንታት ሊሆናቸው ነው፡፡


ከስልጣን የተገለበጡት ፕሬዘዳንት አሁንም በገልባጮቹ እገታ ውስጥ ናቸው ተብሏል፡፡


የኒጀሩ ፖለቲካዊ ቀውስ ያለ ሁነኛ መፍትሄ እንደቀጠለ ነው፡፡



የኔነህ ከበደ


የሸገርንወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2024 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page