top of page
  • sheger1021fm

ታህሳስ 6፣ 2015- በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠየቀ


በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠየቀ።


የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርዓት አፈፃፀም ዙሪያ ያስጠናውን ጥናት ዛሬ በአዳማ ከተማ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ይፋ አድርጓል።


የጥናቱ ውጤት እንዳሳየው የነዳጅ ድጎማ አሰራሩ የተለያዩ ጠንካራ እና ደካማ ውጤቶች ታይተውበታል።


የነዳጅ ብክነትን መቀነሱ እና ተጨማሪ ገቢ ለመንግስት ማስገኘቱ የድጎማ ስርዓቱ ጠንካራ ጎኖች ተብለው ከተነሱት መካከል ናቸው።


የድጎማ አሰራሩ በ1 ወር ብቻ 1 ቢሊየን ብር ግምት ያለው ነዳጅ ከብክነት እንዲድን አግዟል የተባለ ሲሆን ወደ 3.5 ቢሊየን ብር ግምት ያለው ገቢ ለመንግስት አስገኝቷል ተብሏል።


በድጎማ ስርዓቱ አፈፃፀም ዙሪያ ታይተዋል ከተባሉ ችግሮች መካከል ደግሞ አንዳንድ ማደያዎች የነዳጅ እጥረት የተፈጠረ በማስመሰል በህገወጥ መንገድ በእጥፍ ዋጋ ነዳጅ ይሸጣሉ የሚለው ይገኝበታል።


በተሽከርካሪዎች ላይ ያልነበረ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን ወይም ሳልቫቲዮ በመግጠም ድጎማው ለማይመለከተው ወገን ነዳጅ መቅዳት የሚለውም ሌላው ነው።


በአንዳንድ ማደያዎች በቴክኖሎጂ አሰራር ወይም ቴሌ ብር ለመሸጥ ፍላጎት ማጣት ይታያልም ተብሏል።


ስልጣናቸውን ተገን አድርገው ቤተሰቦቻቸውን በህገወጥ የነዳጅ ንግድ የሚያሳትፉ የመንግስት ተሿሚዎች አሉም ነው የተባለው።


በአሽከርካሪዎች በኩል ደግሞ የድጎማ ስርዓቱ ተጠቃሚ ሆነው ለህብረተሰቡ የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት ይልቅ በኮንትራት ስራ ላይ የተሠማሩ እንዳሉ ተጠቅሷል።


ነዳጅ በድጎማ እየገዙ በመንግስት ከተቀመጠው ታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ እንዳሉም ተነግሯል።


በነዳጅ ድጎማ አሰራር ዙሪያ የሚታዩ እነዚህ እና መሠል ችግሮች አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠይቋል፡፡


ንጋቱ ረጋሳ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page