top of page

መስከረም 29፣2017 - የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እና ብሔራዊ መታወቂያ ጽ/ቤት የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ትግበራን በጋራ ሊሰሩ ነው

  • Oct 9, 2024
  • 1 min read

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እና ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ትግበራን በጋራ ሊሰሩ ነው።


በኤጀንሲው በሁሉም ወረዳዎች እና ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በዋና መስሪያ ቤት እና በሁለቱ ቅርንጫፎች የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ምዝገባው ከነገ ጀምሮ ይካሄዳል ተብሏል።


ጉዳዩን አስመልክቶም ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡


ሁለቱ ተቋማት በጋራ መስራታቸው በከተማ ደረጃ የሚከወነውን የፋይዳን የዲጅታል መታወቂያ የምዝገባ ስራ ያፋጣጥናል ተብሎ ታምኖበታል።


ሀሰተኛ ሰነድ መበራከት እና ሌሎች ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመቀነስ ያግዛል የተባለለት ይሄው መታወቂያ ከነገ ጀምሮ ማንኛውም የከተማዋ ነዋሪ በየወረዳው እና በየክፍለ ከተማው በመሄድ ተመዝግቦ የፋይዳ መታወቂያውን መውሰድ ይቻላል ተብሏል።

የንግድ ፍቃድ ለማውጣት የፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ መኖር አስፈላጊ ነው የተባለ ሲሆን ከዚህ በኋላም በባንክ እና ለሌሎች አገልግሎታችን ለመጠቀም መታወቂያው አስፈላጊ እንደሆነ ተነግሯል።


ፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ባዮሜትሪክ እና አሻራ በመሰብሰብ አንድን ሰው መለየት የሚያስችል እና ለሁሉም አገልግሎት ሰጭዎች በኤሌክትሮኒክ መልኩ ደንበኞቻቸውን ማወቅ እንዲችሉ የሚያግዝ ነው ተብሎለታል።


ፋሲካ ሙሉወርቅ


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page