top of page

ነሀሴ 2፣2016 - የገበያ ቅኝት

  • Aug 8, 2024
  • 1 min read


ሰሞኑን የዶላር ዋጋ መጨመሩን ተከትሎ ገበያው ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረ ነው፡፡


አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ የገበያ ስፍራዎች ከዶላር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው ምርቶች ድንገት ዋጋቸው ሲንር ተስተውሏል፡፡


መንግስትም #የዶላር_ጭማሪውን ተገን በማድረግ ዋጋ መጨመር አይቻልም፤ የሚጨምሩት ላይ እርምጃ እየወሰድሁኝ ነው ቢልም በነጋዴዎች ዘንድ ይህ እርምጃ ዋና አከፋፋዮቹን ሳይሆን ቸርቻሪው ነጋዴ ላይ ነው የበረታው ሲሉ እየተቹት ነው፡፡


በችርቻሮ ንግድ ላይ የተሰማሩ #ነጋዴዎች እንዳሉን ከሆነ ምርት አከፋፋይ ነጋዴዎች የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል፤ መንግስት እነሱ ላይ እያደረገው ያለው ቁጥጥር የላላ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ቸርቻሪ ነጋዴው ላይ ግን ቁጥጥሩ እጅግ የበረታ ነው ብለዋል፡፡


ታዲያ መንግስት አሁን እየሰራ ያለው አከፋፋዮችን ከመቆጣጠር ይልቅ ቸርቻሪ ነጋዴው ላይ ነው እየበረታ ያለው ገበያው እንዲረጋጋ ከተፈለገ ቅድሚያ #አከፋፋዮች እና አምራቾችን መከታተልና መቆጣጠር የዋጋ ንረት ችግሩን ይፈታል ብለዋል፡፡


ዘገባውን ለመስራት ከ02 እስከ ላምበረት ስንቀሳቀስ በተመለከትናቸው አብዛኛው ሱቆች ላይ የዘይት ምርት አለመኖሩንም ተመልክተናል፡፡


ጉዳዩን በተመለከተ ነጋዴዎችን ጠይቀን የነበረ ቢሆንም በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሚሰጠን ግን አላገኘንም፡፡


በአካባቢው ቅዳሜና እሁድ የዘይት ምርቶች መግዛታቸውን አንዳንድ ሸማቾች በመረጃ መልክ የነገሩን ሲሆን እጥረቱ ሰሞኑን የተከሰተ ነው ብለውናል፡፡


ምርቱ ከገበያ ከመጥፋቱ በፊት 5 ሊትር #ዘይት ከ1,180 ብር ጀምሮ እተሸጠ እንደነበር ሰምተናል፡፡


በዛሬው ገበያ ላይ አንድ ኪሎ ሽንኩርት ከ60 ብር እስከ 75 ብር ድረስ ተሸጠ ሲሆን ከቅዳሜና እሁድ ገበያ ከፍተኛ ጭማሪ ታይቶበታል፡፡


ድንች በኪሎ 25 ብር ቲማቲም በኪሎ ከ20 ብር እስከ 25 ብር እየተሸጠ መሆኑን ተመልክተናል፡፡



በረከት አካሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች?

ሰኔ 15/2018 ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች? በ2025 ስራውን በ700 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ አደርጋለሁ ብትልም እዛ ማድረስ ግን አልቻለችም ታዲያ ከ አምስት አመት በኋላ እንደቃሏ

 
 
 
የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡

ሰኔ 15/2018 የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡ በእዚሁ ምክንያት የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ግማሽ ያህል ሰራተኞቹን መቀነሱን እና የሰረዘው ፕሮጅክትም መኖሩን መናገ

 
 
 
በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡

ሰኔ 15/2018 በፀረ ተባይ ማምረቻና በሌሎችም ፋብሪካዎች መወገድ ሲኖርባቸው ከ2 እስከ 31 አመት ተከማችተው የሚገኙ አደገኛ ኬሚካሎች ክምችት መኖሩ ተነገረ ፡፡ የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት በተለያዩ ሶስት ፋብሪካዎች ለአካባቢ ብክለት ምክንያት የሚሆኑ ከ69 ቶን በላይ የመጠቀሚያ ጊዜ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page