top of page

ጥር 16፣ 2015-የኩዌት መንግስት የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አቀረበ


የኩዌት መንግስት የስልጣን መልቀቂያ ደብዳቤ አቀረበ፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ አህመድ ናዋፍ የስልጣን መልቀቂያውን እንዳቀረቡ CGTN

ፅፏል፡፡


ካቢኔው የስልጣን መልቀቂያውን ያቀረበው ተቃዋሚዎች ከሚልቁበት ፓርላማ ጋር ባለመግባባቱ ምክንያት እንደሆነ ታውቋል፡፡


የመንግስት የስልጣን መልቀቂያ ማቅረብ በአገሪቱ አጣዳፊ የፓርላማ ምርጫ እንዲካሄድ የሚያስገድድ እንደሆነ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የስልጣን መልቀቂያ ያቀረበው ካቢኔ ሀላፊነቱን የተረከበው በጥቅምት ወር ነበር፡፡


በኩዌት ተሰናባቹ ካቢኔ በ3 ዓመታት ጊዜ 6ኛው እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡


በኩዌት ቀጥሎ የሚካሄደው የፓርላማ ምርጫ በ3 ዓመታት 7ኛው ይሆናል ተብሏል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2024 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page