top of page

የካቲት 30፣2016 - የካፒታል ገበያ ውስጥ መሳተፍ የሚፈልጉ ኩባንያዎችን ለመደገፍ፣ መንገዱን ለማሳየት ሁለት ተቋማት የትብብር ስምምነት አደረጉ

  • sheger1021fm
  • Mar 9, 2024
  • 1 min read

በቅርብ ጊዜ ስራው ይጀምራል ተብሎ በሚጠበቀው የካፒታል ገበያ ውስጥ መሳተፍ የሚፈልጉ ኩባንያዎችን ለመደገፍ፣ መንገዱን ለማሳየት ሁለት ተቋማት የትብብር ስምምነት አደረጉ፡፡


ተቋማቱ ኤም ኤል ኤ(MLA) የተባለው የህግ ቢሮ እና አክሲስ ካፒታል(Axis Capital) ናቸው፡፡


ከ25 ዓመታት በላይ በፕሮጀክት ፋይናንስ እና በድርጅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ በድርጅት እና ግብይት ህግ ስራ ልምድ አለኝ ያለው የምህረተ አብ ልዑል የህግ ቢሮ(ኤም ኤል ኤ) ከአክሲስ ካፒታል ጋር ያሰረው የትብብር ስምምነት የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ስራ ቀና እንዲሆን ያግዛል ተብሏል፡፡


የትብብር ስምምነቱ ዋና ዓላማም ወደ ካፒታል ገበያው መግባት ለሚፈልጉ ኩባንያዎችን መንገዱን ማሳየት ነው ተብሏል፡፡


ንጋቱ ሙሉ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page