top of page

ሰኔ 26፣ 2016 - አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ነብይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

  • Jul 3, 2024
  • 1 min read

አንጋፋው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ነብይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።


ደራሲ ነብይ መኮንን ባደረበት ህመም ምክያት በመኖሪያ ቤቱ ዛሬ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ላይ ህይወቱ ማለፋን ሸገር ከልጁ ራዕይ ነብይ ሰምቷል።


ደራሲ እና ወግ አዋቂው ነብይ ህይወቱ ያለፈው በተወለደ በ68 ዓመቱ ነው።


ነብይ መኮንን ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ መሥራቾች መካከል አንዱ ሲሆን፤ ጋዜጣዋን በዋና አዘጋጅነት መምራቱን የህይወት ታሪኩ ያስረዳል።

የሶስት ሴት ልጆች አባት የሆነው የነብይ መኮንን የቀብር ስርዓት፤ ባለቤቱ እና ልጁ ከውጭ ሀገር ከመጡ ብኋላ እንደሚፈፀም ልጁ ራዕይ ነግራናለች።


"ነገም ሌላ ቀን ነው" የትርጉም ስራ፣ ተከታታይ የግጥም መድብሎች፣ የጉዞ ማስታወሻዎች እንዲሁም የተውኔት ስራዎችን ደራሲ ነብይ መኮንን አሳትሞ ለንባብ አብቅቷል።


ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 በደራሲ ነብይ መኮንን ህልፈት የተሰማውን ሀዘን ይገልፃል።


ለቤተሰቦቹ እና አድናቂዎቹም መፅናናትን ይመኛል።


Recent Posts

See All
በ'ፊንቴክ' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ላይ ፖሊስ የጠየቀው የተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ላይ ለመወሰን ፍርድ ቤት ለነገ ቀጥሯል።

ከ"ፊንቴክ" (Fintech) ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ በከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች ዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ በቀሪ የምርመራ ስራዎች ምክንያት ተጨማሪ 14 ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page