top of page

የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኪር የሱዳኑ ጦርነት ከመቀስቀሱ አስቀድሞ ግጭቱ እንደሚነሳ ያውቁት ነበር ተባለ


ሰኔ 26፣2015


የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኪር የሱዳኑ ጦርነት ከመቀስቀሱ አስቀድሞ ግጭቱ እንደሚነሳ ያውቁት ነበር ተባለ፡፡


የሱዳኑ ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዘዳንት ሳልቫ ኪር ግጭቱ አይቀሬ ስለመሆኑ በደህንነት አማካሪያቸው ቱት ጋትሉአክ ነግረዋቸው እንደነበር ሱዳንስ ፖርት ፅፏል፡፡


ጋትሉአክ ለሳልቫ ኪር እንደነገሯቸው ጦርነቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ መቀስቀሱ በዘባው ተጠቅሷል፡፡


ስለ ጉዳዩ ከደህንነት አማካሪያቸው እንደሰሙ ሳልቫ ኪር የቤተሰብ አባሎቻቸው ከሱዳኗ ርዕሰ ከተማ ካርቱም እንዲወጡ አድርገዋል ተብሏል፡፡


የሱዳን መንግስት ጦር እና RSF የተሰኘው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በውጊያ ላይ መሆናቸው ይታወቃል፡፡



የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page