top of page

'ቪዛ ካርድ' በኢትዮጵያ ጀማሪ ፊንቴኮችን አወዳድሮ ሽልማት ሊሰጥ መሆኑን ተናገረ

  • Sep 13, 2023
  • 1 min read

በአለም ላይ የካርድ ባንኪንግ ከሚሰጡ ቀዳሚ ፊንቴኮች መካከል አንዱ የሆነው VISA ካርድ በኢትዮጵያ ጀማሪ ፊንቴኮችን አወዳድሮ ሽልማት ሊሰጥ መሆኑን ተናገረ፡፡


ከተመሰረተ 60 ዓመት የሞላው VISA ከሶስት ዓመት በፊት ጀምሮ በኢትዮጵያ መስራት መጀመሩ ይታወሳል፡፡


ቪዛ የፋይናንስ እና የባንክ አገልግሎትን አጣምረው የግብይት ሥርዓቱን የሚቀላጥፉ ፊንቴኮችን አወዳድሮ የሚሸልመው ‘’ቪዛ ኤቭሪዌር ኢኒሼቲቭ / Visa Everywhere Initiative’’ ሲል በጠራው ፕሮግራም አማካይነት መሆኑንን ሰምተናል፡፡


የቪዛ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ያሬድ እንዳለ ለሸገር እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ለሚካሄደው ውድድር 170 ፊንቴኮች መሳተፋቸውን፣ ከእዚህም ውስጥ አምስቱ መለየታቸውን አስረድተዋል፡፡


አምስቱ የመጨረሻዎቹ እጩዎች ካቻ፣ ላኪፔይ፣ ቀና፣ ስማይል ፔይ እና መርካቶ ፋይናንስ መሆናቸው ዳይሬክተሩ ነግረውናል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page