በአለም ላይ የካርድ ባንኪንግ ከሚሰጡ ቀዳሚ ፊንቴኮች መካከል አንዱ የሆነው VISA ካርድ በኢትዮጵያ ጀማሪ ፊንቴኮችን አወዳድሮ ሽልማት ሊሰጥ መሆኑን ተናገረ፡፡
ከተመሰረተ 60 ዓመት የሞላው VISA ከሶስት ዓመት በፊት ጀምሮ በኢትዮጵያ መስራት መጀመሩ ይታወሳል፡፡
ቪዛ የፋይናንስ እና የባንክ አገልግሎትን አጣምረው የግብይት ሥርዓቱን የሚቀላጥፉ ፊንቴኮችን አወዳድሮ የሚሸልመው ‘’ቪዛ ኤቭሪዌር ኢኒሼቲቭ / Visa Everywhere Initiative’’ ሲል በጠራው ፕሮግራም አማካይነት መሆኑንን ሰምተናል፡፡
የቪዛ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ያሬድ እንዳለ ለሸገር እንደተናገሩት በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ለሚካሄደው ውድድር 170 ፊንቴኮች መሳተፋቸውን፣ ከእዚህም ውስጥ አምስቱ መለየታቸውን አስረድተዋል፡፡
አምስቱ የመጨረሻዎቹ እጩዎች ካቻ፣ ላኪፔይ፣ ቀና፣ ስማይል ፔይ እና መርካቶ ፋይናንስ መሆናቸው ዳይሬክተሩ ነግረውናል፡፡
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Commentaires