top of page

ሐምሌ 29፣2015 - የኒጀር የመንግስት ገልባጮች ሀገሪቱ ከተለየያ ሀገራት ጋር የነበራትን ግንኙነት አቋረጡት

የኒጀር ወታደራዊ የመንግስት ገልባጮች ሀገሪቱ ከአሜሪካ፣ ከፈረንሳይ፣ ከናይጀርያ እና ከቶጎ ጋር የነበራትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጡት፡፡


የኒጀሮቹ ገልባጮች ህጋዊውን የፕሬዘዳንት ሞሐመድ ባዙምን መንግስት ወደ ሀላፊነቱ እንዲመልሱ ግፊት እንደበረታባቸው አናዶሉ ፅፏል፡፡


በዚሁ ጉዳይ የኒጀሮቹን የመንግስት ገልባጮች ለማነጋገር ወደ ሀገሪቱ አምርቶ የነበረው የምዕራብ አፍሪካ መንግስታት ምጣኔ ሐብታዊ ማህበር /ኢኮዋስ/ የልዑካን ቡድን ያለ አንዳች ውጤት መመለሱ ታውቋል፡፡


ኤኮዋስ ገልባጮቹ የባዙምን መንግስት ወደ ሀላፊነቱ እንዲመልሱ የሰጣቸው የ7 ቀናት የማስጠንቀቂያ ገደብ ነገ ያበቃል፡፡


የናይጀሪያው ፕሬዘዳንት ቦላ ቱኑቡ የሀገሪቱ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት /ሴኔት/ የናይጀሪያ ጦር ወደ ኒጀር እንዲዘምት ይሁንታውን እንዲያረጋግጥ መጠየቃቸው ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz


Website: https://www.shegerfm.com/


Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2024 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page