top of page

በሴቶች ተይዘው የነበሩ የከፍተኛ ስልጣን ቦታዎች ተመልሰው በወንዶች እየተያዙ መሆኑን ጥናት አሳየ፡፡

  • sheger1021fm
  • 1 day ago
  • 1 min read

ህዳር 2 2018

ሴቶች በሰላምና ደህንነት ጉዳዮች እንዲወያዩ፣ መፍትሄም እንዲሰጡ የማድረግ ጅምሮች ቢኖሩም አሁንም ብዙ እንደሚቀር ጥናት አሳየ፡፡


በሴቶች ተይዘው የነበሩ የከፍተኛ ስልጣን ቦታዎች ተመልሰው በወንዶች እየተያዙ መሆኑን በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡


ላለፉት 25 ዓመታት ሴቶች በሰላምና ደህንነት ላይ የነበራቸው ተሳትፎና ሚና ምን ይመስላል የሚለው ጥናት ያደረጉት በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሦስተኛ ዲግሪያቸውን በመስራት ላይ የሚገኙት አቶ መብራቱ ጌርጌሶ ናቸው፡፡


አሁን ላይ ሴቶች በፖለቲካው በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ በሌሎችም ጉዳዮች ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም በቂ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡


በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ መምህርት የሆኑት ሙሉእመቤት ማጆሮ(ዶ/ር) ሴቶች በባህላዊ የሰላም ግንባታ ላይ ተሳትፎቸው ምን ይመስላል የሚለው ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡


በባህላዊ የሰላም ግንባታ ላይ የከፍተኛ ሚና ቢኖራቸውም እንደሰሩ አይቆጠርላቸውም ሲሉ ነግረውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page