top of page

30፣2016 - ዓባይ ባንክ 7 ሚሊዮን ብር ያወጣበትን አዲሱን የንግድ ምልክት ይፋ አደረገ

  • sheger1021fm
  • Mar 9, 2024
  • 1 min read

ባንኩ ነባሩን የንግድ ምልክት እና መገለጫ የቀየረው በተለየ መልኩ የደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት እና ለእድገት እና ለፈጠራ ያለውን ትጋት ለማስረዳት በማሰብ ነው ተብሏል።


የባንኩን አዲስ መለያ የተዘጋጀው በአቶ ያየህይራድ ታደሰ እና በስቱዲዮኔት እንደሆነ ተነግሯል፡፡


ለስራውም 7 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ተብሏል።


አዲሱ የንግድ ምልክት የዓባይ ወንዝ ዋና መገለጫ ከሆነው የጢስ ዓባይ ፏፏቴ የተነሳ እና በሰባት አራት ማዕዘናዊ ቋሚ መስመሮች የተወከለ መሆኑን ተጠቅሷል።


ይህም የባንኩን እድገት፣ ችግሮችን የመቋቋም አቅም፣ አስተማማኘነት እና ታማኘነት ያመለክታል ሲባል ሰምተናል፡፡

የባንኩ የመለያ መገለጫ ሆኖ ሲያገለግል የነበረው ታማኝ አገልጋይ ወደ "Source of Greatness" መቀየሩንም ሰምተናል።


የእንግሊዝኛው አቻ የአማርኛ ፍቺም እየታሰሰበት ነው ተብሏል።



አዲሱ የንግድ ምልክት መገለጫው የደንበኞቹ ትልቅ የመሆን ተስፋ፣ ምኞት እና እቅድ ምንጭ በመሆን፤ ወደ ከፍታ ለመድረስ በሚደረግ ጉዞ የማያለሰልስ የባንኩን የፋይናንስ ድጋፍ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተነግሯል፡፡


ዓባይ ባንክ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ሀብቱ 60 ቢሊዮን ብር፣ የተቀማጭ 48.6 ቢሊዮን ብር፣ የተከፈለ ካፒታል 5.8 ቢሊዮን ብር ፣ አጠቃላይ ካፒታሉ 8.7 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተነግሯል።


ከ533 በላይ ቅርንጫፎች እና 3.2 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችም አሉኝ ብሏል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page